Friday, May 5, 2017

ጥቂት ስለአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊ አርበኛ ሃና – ከጋዜጠኛ መሳይ መኮንን


የማህሌትንና የኤዶምን ከህወሀት ማጎሪያ እስር ቤት ነጻ መሆን ውስጤ የፈጠረውን ደስታ እያጣጣምኩ እያለ ድንገት በትዝታ አምስት ወራት ወደ ሁዋላ ሄድኩኝ- -ከኤርትራ በረሃ:: ይህቺን ኢትዮጵያን ከህወሀት እስር ቤት ነጻ ለማውጣት ብረት ያነሳችውን እህታችንን ላስተዋውቃችሁ::
አርበኛ ሀና ትባላለች:: የ23 ዓመት ወጣት ናት:: የአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊ ወታደር ስትሆን በተለያዩ አውደ ውጊያዎች ተሳትፋለች:: በኤርትራ በረሃ ስማቸው ከጀግንነት ጋር ከሚነሳላቸው አርበኞች መሃል ሀና ግንባር ቀደም ናት:: ስሟ በአርበኞች መንደር ገኖ ይነሳል::
………አንድ ጊዜ ላይ እንዲህ ሆነ::
ሀና የምትገኝበት ወታደራዊ ክፍል ግዳጅ ይሰጠዋል:: እስከ 30 የሚጠጋ አርበኛ የሚገኝበት ይህ ቡድን የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጦ በመግባት በአንድ የህወሀት ወታደራዊ ካምፕ ላይ ጥቃት ፈጽሞ የመመለስ ግዳጅ ተሰጥቶት ይሰማራል:: ሀና መትረየሷን ታጥቃለች:: ጠዋት ከመነሻቸው ወደ ኢላማ ቦታው ገሰገሱ:: እንደታቀደው ድንገተኛ ጥቃቱ ተሰንዝሮ የታሰበውን ጉዳት አድርሰው ወደ ካምፓቸው ሊመለሱ እያለ ድንገት በህወሀት ሰራዊት ይከበባሉ:: ምን ይደረግ? ብዙ ቁጥር ያለውንና እስከአፍንጫው የታጠቀውን የህወሀት ሰራዊት መክቶ ወደ ካምፕ መመለስ ከባድ ሆነ:: የዚህን ጊዜ ነበር አንድ ጀግና ታሪክ የሰራችው:: ….ሀና::
መትረየሷን መተረች:: ገዢ መሬት ያዘች:: ቦታዋን አስተካከለች:: ….እሷ መስዋዕት ሆና የትግል ጓዶቿን ልታስመልጥ ወሰነች:: ምሽት እየመጣ ነው:: ጓዶቿ ተስናበቷት:: ዳግም በህይወት እንደማያገኟት ታወቃቸው:: …እሷ መትረየሷን ወደ ህወሀት ሰራዊት ለቀቀችው:: ለጓዶቿ ሽፋን በሚሰጥ ስልት አስካካችው:: …ፍልሚያው በአንዲት ሀና እና በህወሀት ሰራዊት መሃል ሆነ:: የሀና መትረየስ ያስካካል:: ጓዶች በዚያ ሽፋን ወደ ጦር ካምፓቸው እየተመለሱ ነው:: የሀና የመትረየስ ድምጽ እየራቃቸው ነው:: እነሱ ይተርፉ ዘንድ አንድ አርበኛ መስዋዕት መሆን ግድ አለ:: በተሰጣቸው ግዳጅ ውጤታማነት እየተደሰቱ የሃናን መስዋዕትነት እያወደሱ ከካምፓቸው ምሽት ላይ ደረሱ:: በአርበኞች መንደር ህይወት እንዲህ ናት:: ታጋይ ይሰዋል:: ትግል ይቀጥላል::
…እኩለ ሌሊት ከመድረሱ በፊት ነው:: ጭው ካለው የኤርትራ በረሃ አንድ ሰው ወደ አርበኞቹ መንደር ከኢትዮጵያ ድንበር አቅጣጫ ይገሰግሳል:: በርቀት የተመለከቱት የሌሊት የካምፕ ተረኛ ዋርዲያዎች(ጠባቂዎች) መሳሪያቸውን አስተካክለው ጣት ከቃታ አገናኝተው ወደ ካምፑ እየገሰገሰ ያለውን ሰው ይጠብቃሉ:: ውድቅት ሌሊት ስለነበር ማንነት መለየት አልተቻለም:: የሚገሰግሰው ሰው እየቀረበ ሲመጣ ዋርዲያዎቹም ኢላማቸውን አስተካክለው እርምጃ ለመውሰድ ተዘጋጁ:: ….ሰውዬው ቀረበ:: ሴት ናት::ሃና:: ዋርዲያዎቹ አላመኑም:: የዕለቱን የይለፍ ቃል ጠየቋት:: መለሰችላቸው:: ደክሟታል:: ተአምር የሚያሰኘው ከዚይ የህወሀት ሰራዊት ከበባ ማምለጧ አይደለም:: ሁለት የጦር መሳሪያዎችንም ማርካ ተሸክማለች:: ከሷ መትረየስ ጋር ሶስት:: ዋርዲያዎቹ በሚያዩት ነገር ተደንቀዋል:: በአርበኞች መንደር ስለ ሃና እርም ወጥቷል:: ጉድ ተባለ::
….ሃናን በአካል ሳገኛት በጣም ቁጥብ ነበረች:: ብዙ አትናገርም:: ታሪኳን እንድታጫውተኝ ያደረኩት ጥረት አልተሳካም:: ሲበዛ ዝምተኛ ናት:: ጀግና አይናገርም::
…ሃና ከሰሞኑ ውጊያዎች በአንዱ እንደተሰለፈች እገምታለሁ:: ልብን በኩራት በሚያሞቀው ጀግንነቷ ሁሌም አስታውሳታለሁ:: የጣይቱ ልጅ!!!!!

የነፃነት ሃይሎች ድንገተኛ ጥቃቶች እየሰነዘሩ ከፍተኛ ኪሳራ እያደረሱ ነው ተባለ


የነፃነት ሃይሎችን ወታደራዊ ና የተጠና ስልታዊ የደፈጣ ጥቃት መቆጣጠር ያቃተው የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ዘረኛ ቡድን በድንበር አካባቢ የነፃነት ሃይሎችን የደፈጣ ጥቃት ለመቆጣጠር ባለመቻሉ ወደ ድንበር አካባቢ ተጨማሪ ጦር ያስጠጋ ሲሆን ለሱዳን ተቆርሶ በተሰጠው የኢትዩጲያ መሬት ላይ ከሱዳን ወታደሮች ጋር በመሆን የጥምር ጦር እየመሰረተ ባለበት በዚህ ወቅት በሰሜን ጎንደር፣ በጎጃም ጃዊ ፣ በቤንሻንጉል አካባቢወች የነፃነት ሃይሎች ድንገተኛ ጥቃቶች እየሰነዘሩ ከፍተኛ ኪሳራ እያደረሱበት ይገኛል።
በቤንሻንጉል ሸርቆሌ የወርቅ ማውጫ ሰፍሮ በሚገኝ የህወሓት ጦር ሃይል ውስጥ በቅርብ ርቀት በጫካ ውስጥ በቅኝት ላይ ከነበሩት 8 ወታደሮች ላይ ባነጣጠረው የቀስት ጥቃት 5ቱ በእባብ መርዝ በተቀጠቀጠ ቀስት ተወግተው ወዲያውኑ ለሞት ተዳርገዋል።
ቀሪወቹ 3ቱ ወታደሮችም ውስጥ በአንዱ በጀርባው በያዘው ኮሮጆ ተሰንቅሮበት እግሬ አውጭኝ ብሎ ያመለጠ ሲሆን በአንደኛው በእግሩ ላይ ተወግቶ ደቂቃወችን የቆየ ወታደር እራሱን ለመከላከል በተኮሰው ጥይት አንድ ቀስተኛ ያቆሰለ ሲሆን መሳሪያም እንደተማረኩ ታውቋል።
ይህ ቀስት ሲቀጠቀጥ በከፍተኛ መርዛማ እባቦች መርዝ እንደመሰራቱ የተወሰነ አካሉን ከበሳው ወዲያውኑ መርዞ የመግደል ሃይል እንዳለው ታውቋል።
ከዚህ ጥቃት በኃላ ዙሪያ አካባቢወች እየተፈተሹ ሲሆን ምንም ነገር ሊያገኙ አለመቻላቸው የአገዛዙን ወታደራዊ አዛዦች አስደንግጧል።
ከሰሞኑ በተለያዩ አካባቢወች በደረሰ የቀስት ጥቃት የአገዛዙ ሹመምንት ፣ሚኒሻወች ቤት ለቤት የቀስት ብርበራ እያደረጉ ይገኛል።
በገበያ ቀኖች በከተሞች መውጫ መግቢያ አካባቢ ከፍተኛ ፍተሻ እያደረጉ እንደሚገኝ ተረጋግጧል።

Sunday, April 23, 2017

የአሜሪካ ኮንግረስ ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ሕጎች ረቂቆችን እያወጣ ነው


hqdefault
በዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት ኢትዮጵያን በተመለከተ የሚቀርቡ የውሣኔ ሀሳቦችን «በተሳካ ሁኔታ አምክኛለሁ» ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት ቢናገርም ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ህጎች አሁንም በኮንግረሱ እየረቀቁ መሆናቸውን የህዝብ ተወካዮች አመልክተዋል።
የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ወርቅነህ ገበየሁ በመጋቢት መጨረሻ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ሁለት ረቂቅ ህጎችን እንዳጨናገፈ የሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
የኮንግረሱ የአፍሪካ ንዑስ ኮሚቴ ሊቀመንበር ለዝግጅት ክፍላችን በሰጡት ማብራሪያ «ኮንግረስ በምርጫ ሲቀየር ህጎች እንዳዲስ ለውሳኔ ይቀርባሉ እንጂ የተጨናገፈም ሆነ እንዲዘገይ የተደረገ ህግ የለም» ብለዋል።
ሙሉው ዘገባ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ኦፌኮ’ ህልውናው ሊያከትም ነው ፤ የምርጫ ቦርዱ ፕሮፌሰር በቃና ታሪካዊ ውሳኔ ይጠበቃል


በኦሮሚያ ሰፊ ድጋፍ ያለው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ኦፌኮ ህልውናውን ጠብቆ የመቆየት እድል እንደሌለው ለምርጫ ቦርድና ለስርዓቱ ቅርበት ያላቸው የኦህዴድ ሰዎች ለዛጎል ገለጹ። እንደ ገለጻው ኦፌኮ እንደ ፓርቲ እንዲቆይ የማይፈለገው በሁለት አበይት ምክንያቶች ነው።
የመጀመሪያው ከኦነግ በሁዋላ ኢህአዴግን የፈተነው ኦፌኮ በመሆኑና ሰፊ ድጋፍ ስላለው በዚህ መልኩ ሕዝብ የሚደግፈው ድርጅት በተለይ ኦሮሚያ ላይ እንዲኖር ስለማይፈለግ ነው። ሁለተኛው ምክንያት ቀጣዩን ምርጫ ኦሮሚያ ላይ ማሸነፍ ስለማይቻል ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ በሚል እንደሆነ የመረጃው ባለቤቶች ያስረዳሉ። በሌላም በኩል ከድርድር የወጣው መድረክም ኦፌኮን ካጣ ባዶ እንደሚሆን በማሰብም ጭምር ነው ሲሉ ያክላሉ።
ኢህአዴግ ያቋቋመውንና በቀደሞው የምርጫ ቦርድ ሹም የሚመራው የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ያቀረበውን ሪፖርት ያስታውሱት ክፍሎች፤ በሪፖርቱ ከተወነጀሉት ሶስት ፓርቲዎች መካከል ኦፌኮ አንዱ መሆኑን ይታወሳል። ሰማያዊ ፓርቲና የጌዲዮ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እና ኦፌኮ በኦሮሚያና በአማራ ክልል የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ “እንዲቀሰቀስና እንዲባባስ አድርገዋል” በሚል የቀረበውን ሪፖርት ሸንጎው አጽድቆ ፓርቲዎች እንዲከሰሱ ወሳኔ አስተላልፎ እንደነበር የሚታወስ ነው።
ለገለልተኛ አጣሪዎችና ለተባበሩት መንግስታት መርማሪዎች በሩን የዘጋው ኢህአዴግ፣ ሕዝባዊ አመጹን ተከትሎ ለጠፋው የሰው ህይውት ነጻና ገለልተኛ አጣሪዎች ምርመራ እንዳያደርጉ ሲከለክል ምክንያት አቅርቦ ነበር። ምክንያቱም ” ሉአላዊነትን የማስደፈር ያህል ነው” የሚል ነበር። ኢህአዴግ ይህንን ቢልም በአገሪቱ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ተጥሶባቸዋል የሚባሉ አካባቢዎችን ለጋዜጠኞች፣ ለለጋሽ አካላትና ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ለምልከታ ሲከለክል ይህ የመጀመሪያው እንዳልሆነ የሚገልጹ አሉ።
የዜናው ሰዎች እንደሚሉት ኢህአዴግ የሚፈራው ከውጪ ያሉ ተቃዋሚዎችን አይደለም። የአንድ ከፍተኛ ባለስልጣን ስም በመጥራት እነዚሁ ክፍሎች እንደተናገሩት ኢህአዴግ አገር ቤት ተነስቶ የነበረው ተቃውሞ አይነት ቀውስ በድጋሚ እንዳይፈጠር “የተኛውንም ርቀት” ይሄዳል። ከተፈጠረም በየትኛውም ወቅትና ሰዓት የወታደራዊ መንግስት ለማወጅና አገሪቱን “በይፋ” በወታደራዊ ስር ለማሰተዳደር ዝግጁ ነው።
በዚሁ መነሻ በኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን በአብዛኛው የአገሪቱ ሕዝብ ተቀባይነት ያላቸውን የኦፌኮን መሪዎችና ራሱን ፓርቲውን አግዶ ህልውናውን ማክሰም ሆን ተብሎ ሲሰራበት የነበረ ጉዳይ ነው። ይህንኑ እቅድ ተግባራዊ ለማደረግ ደግሞ ” ህግ” የሚባለውን ማደናገሪያ መጠቀም ግድ በመሆኑ ገለልተኛ እንዳልሆነ በየተኛውም የህብረተሰብ ክፍል የሚታወቀውን የ” ኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ጉባኤ” ሪፖርት መጠበቅ ግድ ነበር። ዜናውን የጠቆሙት የኦህዴድ ሰዎች ” ክስ እንዲመሰረት የተወሰነባቸው ፓርቲዎች ሲከሰሱ በጥቅሉ ምን እንደሚወሰንባቸው ባይታወቅም ኦፌኮ ግን እንደሚታገድና፣ የምርጫ ቦርድ የእውቅና ማስረጃን እንደሚነጠቅ፤ በዛውም እንደሚከስም፣ ሌላ ሕዝብ የሚያምናቸው ድርጅቶች እስኪበቅሉ ምርጫውም ያልፋል ” ብለዋል።
ዶክተር መረራ ጉዲና፣ በቀለ ገርባ ፣ ያለተዘመረለት ኦልባና ሌሊሳ እና በርካታ አመራሮቹን፣ አባላቱን፣ ደጋፊዎቹ እስር ላይ ያሉት ኦፌኮ መጪው ዕድሉ እንደተባለው መክሰም ከሆነ ይህንን ወሳኔ የሚወስኑት ፕሮፌሰር በቃና – የምርጫ ቦርድ “ዋና ሃላፊ” መሆናቸው ታሪኩን፣ አጋጣሚውን፣ እንዲሁም ውሳኔውን ልዩ እንደሚያደርገው ከኦህዴድ ሰዎች የተገኘው ዜና ያስረዳል።
የሰብአዊ መብት ኮሚሽኑንን ሪፖርት በተለያየ መልኩ ከመዘገብ ውጪ በኦፊሳል የተጠቀሱት ፓርቲዎች ላይ ምን ዓይነት እርምጃ እንደሚወሰድ የተባለ ነገር የለም። ይሁንና ተጠያቂ እንዲደረጉ መወሰኑ የዜናውን ተአማኒነት ያጎላዋል የሚል እምነት አለ። ኦፌዴን ሰማያዊ ፓርቲና የጌዲዮ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት የተወሰነባቸውን ውሳኔ አስመልክቶ የሰጡት ” በገለልተኛ ወገን ያልቀረበ ሪፖርት ተቀባይነት የለውም” ሲሉ መመለሳቸው አይዘነጋም።

የዶ/ር መረራ ፓርቲ ቀደም ሲል ስሙ ተነጥቆ ለአቶ ቶለሳ ቢሰጥም በአጭር ጊዜ ውስጥ ክርክሩን አቁመው ኦፌኮን ማቋቋማቸው አይዘነጋም። ኢህአዴግ የሚወዳደረው ፓርቲ ሲፈጠር ስሙን መንጠቅና ለሌላ አሳልፎ የምስጠት፣ አመራሮቹን አስሮ የማዳከም ለዩ ባህሪው እንደሆነ በስፋት የሚከሰስበት ጉዳይ ነው። አሁን በድርድር ላይ ያሉትን ፓርቲዎች ታሪክ ማየትም ይህንኑ ሃቅ ያጎላዋል።88c6732c

Friday, April 21, 2017

የአርበኞች ግንቦት7 አባላት የሆኑ ታጋዮች በደምቢያ ወረዳ ሰረባ መስኖ አጠገብ ሌሊት ላይ ጥቃት ፈጽመው


2 ገልባጭ መኪኖችና አንድ እስካቫተር መኪና የተቃጠሉ ሲሆን፣ በታጋዮች እና ድርጅቱን በሚጠብቁት መካከል ለ30 ደቂቃ ያክል የተኩስ ልውውጥ መካሄዱንና አንድ ወታደር መገደሉን ድርጅቱ ለኢሳት በላከው መረጃ አስታውቋል።
ኢሳት ወደ አካባቢው ነዋሪዎች ስልክ በመደወል በመኪኖች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ሲያረጋግጥ፣ በሰው ህይወት ላይ ስለደረሰው ጉዳት ግን ማረጋገጫ ሊያገኝ አልቻለም። የአይን እማኞች ጉራምባ ቀበሌ ላይ በተለይም በቀበሌው ሊቀመንበር አቶ መንግስቱ መኖሪያ ቤት አካባቢ ከፍተኛ የተኩስ ለውውጥ መካሄዱን ገልጸዋል።
አካባቢው በወታደሮች ቁጥጥር ስር በመውደቁ የተቃጠሉትን መኪኖች ብዛት በትክክል ለማወቅ እንዳልቻሉ፣ ነገር ግን 3 መኪኖች ጠዋት ላይ ተቃጥለው ማየታቸውን ተናግረዋል።
ወደ አካባቢው የተንቀሳቀሱት ወታደሮች የአካባቢው ሚሊሺያ እርምጃ ባለመውሰዱ መሳሪያቸውን እየቀሙ እያሰሩዋቸው ነው። በሌላ በኩል ትናንት ምሽት በጎንደር ከተማ ተጨማሪ የቦንብ ጥቃት የተፈጸመ ሲሆን፣ አንድ ታጣቂ ግለሰብ ጥቃቱን ባደረሱት ሃይሎች ተመትቶ ጉዳት ደርሶበታል፡፡
ጥቃቱ በቀጠናው የህወሃት ወኪል በመሆን የደህንነት ስራ ይሰራል በተባለው በአቶ አማረ አምባየ ላይ ያነጣጠረ እንደነበር ለኢሳት የደረሰው መረጃ ያሳያል። ግለሰቡ እና ጠባቂው ጉዳት ደርሶባቸው ለህክምና ወደ አዲስ አበባ መላካቸውንም መረጃው አክሎ አመልክቷል።
ጥቃቱን ተከትሎ ከሙሴ ባምብ ወታደራዊ ካምፕ የተንቀሳቀሰ አንድ ኦራል መኪና ከምሽት 5 ሰአት አካባቢ ልዩ ስሙ የኢትዮጵያ ካርታ በሚባለው ስፍራ ላይ በጥይት ተመትቶ ሲገለበጥ 4 ወታደሮች ወዲያውኑ ህይወታቸው ሲያልፍ፣ 5 ወታደሮች ደግሞ ቆስለዋል።
መኪናው ዛሬ ተጎትቶ ጎንደር አዘዞ ወደሚገኘው ወታደራዊ ካምፕ ተወስዷል። የቆሰሉ ወታደሮችም አዘዞ በሚገኘው የጦር ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ሲሆን፣ ሟች ወታደሮችም አዘዞ ሎዛ ማሪያም ቤ/ክርስቲን ተቀብረዋል፡፡
የአሁኑ ጥቃት በአንድ ሳምንት ጉዜ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ መፈጸሙ ነው። በሰራባ የመስኖ ፕሮጀክት አካባቢ ተደጋጋሚ ጥቃቶች የተፈጸሙ ሲሆን፣ ጥቃቱን በሚያደርሱ ታጋዮች ላይ እስካሁንም ምንም ጉዳት አልደረሰባቸውም።
ገዢው ፓርቲ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አማካኝነት ማንኛውንም አይነት የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተቆጣጥሬዋለሁ ቢልም፣ አሁንም በሰሜን ጎንደር የተለያዩ ወረዳዎች ጥቃቶች እየተፈጸሙ ነው።

ጎንደር አስረኛውን የቦንብ ፍንዳታ ትናት አስተናገደች


በጎንደር ከተማ በቀበሌ 15 ቀጠና 1 ፋሲለደስ እስታዲየም አካባቢ ነዋሪ የሆነው የሆነው የህውሀት የሰሜን ጎንደር ፣ የደቡብ ጎንደር ፣ የምእራብ ጎጃም የአካባቢው ማለትም የቀጠናው የህውሀት ሰብሳቢ ሊቀምንበር እና የትግራይ ልማት ማህበር ሊቀመንበር የሆነው አምባየ አማረ በተባለው ግለሰብ ሚያዚያ 12 ቀን 2009 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡47 ሰዓት ሲሆን መኖሪያ ቤቱ በቦምብ ጥቃት ተፈፅሞበታል ፡፡
ይህ በንዲህ እንዳለ በትላንትናው እለት በጎንደር የተፈጠረውን ችግር ለማረጋጋት ከሙሴ ባምብ ወታደራዊ ካምፕ ወታደር ጭኖ የተንቀሳቀሰ አንድ ኦራል መኪና ምሽት 4፡40 ላይ ልዩ ስሙ የኢትዮጵያ ካርታ የሚባለው ቦታ ላይ በጥይት ተመትቶ መኪናው ሲገለበጥ 4 ወታደሮች ወዲያውኑ ሲሞቱ 5 ቀላል ቁስለኛ ሆነዋ ኦራል መኪናው ዛሬ 13/08/2009 ከቀኑ 5 ፡ 00 ሰዓት ተጎትቶ ወደ ጎንደር አዘዞ ወደሚገኘው ወታደራዊ ካምፕ የመጣ ሲሆን የቆሰሉ ወታደሮች አዘዞ በሚገኘው የጦሩ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛሉ ሟቾችም አዘዞ ሎዛ ማሪያም ቤ/ክርስቲን ተቀብረዋል፡፡