Friday, May 5, 2017

የነፃነት ሃይሎች ድንገተኛ ጥቃቶች እየሰነዘሩ ከፍተኛ ኪሳራ እያደረሱ ነው ተባለ


የነፃነት ሃይሎችን ወታደራዊ ና የተጠና ስልታዊ የደፈጣ ጥቃት መቆጣጠር ያቃተው የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ዘረኛ ቡድን በድንበር አካባቢ የነፃነት ሃይሎችን የደፈጣ ጥቃት ለመቆጣጠር ባለመቻሉ ወደ ድንበር አካባቢ ተጨማሪ ጦር ያስጠጋ ሲሆን ለሱዳን ተቆርሶ በተሰጠው የኢትዩጲያ መሬት ላይ ከሱዳን ወታደሮች ጋር በመሆን የጥምር ጦር እየመሰረተ ባለበት በዚህ ወቅት በሰሜን ጎንደር፣ በጎጃም ጃዊ ፣ በቤንሻንጉል አካባቢወች የነፃነት ሃይሎች ድንገተኛ ጥቃቶች እየሰነዘሩ ከፍተኛ ኪሳራ እያደረሱበት ይገኛል።
በቤንሻንጉል ሸርቆሌ የወርቅ ማውጫ ሰፍሮ በሚገኝ የህወሓት ጦር ሃይል ውስጥ በቅርብ ርቀት በጫካ ውስጥ በቅኝት ላይ ከነበሩት 8 ወታደሮች ላይ ባነጣጠረው የቀስት ጥቃት 5ቱ በእባብ መርዝ በተቀጠቀጠ ቀስት ተወግተው ወዲያውኑ ለሞት ተዳርገዋል።
ቀሪወቹ 3ቱ ወታደሮችም ውስጥ በአንዱ በጀርባው በያዘው ኮሮጆ ተሰንቅሮበት እግሬ አውጭኝ ብሎ ያመለጠ ሲሆን በአንደኛው በእግሩ ላይ ተወግቶ ደቂቃወችን የቆየ ወታደር እራሱን ለመከላከል በተኮሰው ጥይት አንድ ቀስተኛ ያቆሰለ ሲሆን መሳሪያም እንደተማረኩ ታውቋል።
ይህ ቀስት ሲቀጠቀጥ በከፍተኛ መርዛማ እባቦች መርዝ እንደመሰራቱ የተወሰነ አካሉን ከበሳው ወዲያውኑ መርዞ የመግደል ሃይል እንዳለው ታውቋል።
ከዚህ ጥቃት በኃላ ዙሪያ አካባቢወች እየተፈተሹ ሲሆን ምንም ነገር ሊያገኙ አለመቻላቸው የአገዛዙን ወታደራዊ አዛዦች አስደንግጧል።
ከሰሞኑ በተለያዩ አካባቢወች በደረሰ የቀስት ጥቃት የአገዛዙ ሹመምንት ፣ሚኒሻወች ቤት ለቤት የቀስት ብርበራ እያደረጉ ይገኛል።
በገበያ ቀኖች በከተሞች መውጫ መግቢያ አካባቢ ከፍተኛ ፍተሻ እያደረጉ እንደሚገኝ ተረጋግጧል።

No comments:

Post a Comment