Monday, October 24, 2016

አሜሪካ በኢትዮጵያ ጉዞ ላይ ማስጠንቀቂያ አወጣች


የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ከትናንት በስተያ ምሽት ላይ ባወጣው ማስጠንቀቂያ ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ አማራና ኦሮምያ ክልሎች ውስጥ በቀጠለው ለብዙ ሕይወት መጥፋት፣ በሺሆች ለሚቆጠሩ ሰዎች መታሠርና መጎዳት እንዲሁም ለተከታታይ የንብረት ውድመትን ምክንያት በሆነው አለመረጋጋት ምክንያት አሜሪካዊያን ወደ ኢትዮጵያ ለማድረግ የያዙትን እጅግ አስፈላጊ ያልሆነ የጉዞ ውጥን ሁሉ እንዲሠርዙ አሳስቧል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በሃገሪቱ ውስጥ ባለው የፀጥታ ሁኔታ ምክንያት የአሜሪካ ኤምባሲ በብዙ የሃገሪቱ ክፍሎች ውስጥ የቆንስላ አገልግሎት ለመስጠት ያለው ችሎታ የተወሰነ መሆኑንም ይኸው የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አመልክቷል፡፡
የኢትዮጵያ መንግሥት ከመስከረም 28/2009 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መደንገጉን መግለጫው አስታውሶ ጥቅምት 5/2009 ዓ.ም በወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እርምጃዎች አፈፃፀም መመሪያ መሠረት ግለሰቦች ወትሮ የተፈቀዱ የነበሩ ግንኙነት ማድረግን፣ መገናኛ ብዙኃንን መከታተልን፣ በስብሰባዎች ላይ መሣተፍን፣ ከሌሎች መንግሥታት ወይም ከውጭ ድርጅቶች ጋር ግንኙነቶችን ማድረግን፣ የሰዓት እላፊ ገደብን መጣስን የመሳሰሉ ተግባራት ውስጥ ቢገኙ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሊታሠሩ እንደሚችሉ አሳስቧል፡፡
መመሪያው የዩናይትድ ስቴትስና የሌሎችም ሃገሮች ዲፕሎማቶች ለመንግሥት ቀድመው ሳያሳውቁና ፍቃድ ሳያገኙ ከአዲስ አበባ ከአርባ ኪሎ ሜትር ርቀት ዘልቀው እንዳይጓዙ የሚከለክል መሆኑ የአሜሪካ ኤምባሲ ለዜጎቹ ድጋፍ ለመስጠት ያለውን አቅም በብርቱ እንደሚጎዳው መግለጫው አስረድቷል፡፡ የአስቸኳይ ጊዜ መመሪያው ሙሉ ቃል በአሜሪካ ኤምባሲ ዌብ ሳይት ላይ ሠፍሮ እንደሚገኝም አስታውቋል፡፡
የኢንተርኔት፣ የሞባይል ዳታና የስልክ አገልግሎቶች በመላ ሃገሪቱ ውስጥ በየወቅቱ ወይም ሙሉ በሙሉ የሚቋረጡ መሆናቸውም ኤምባሲው ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎች ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት የሚያስተጓጉል መሆኑንም የጉዞ ማስጠንቀቂያው አመልክቷል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ በሚቆዩበት ጊዜ ዜጎቹ አማራጭ የግንኙነት ዝግጅቶች እንዲኖሯቸውና ያለውን ሁኔታም ለቤተሰብና ለወዳጆቻቸው እንዲያሳውቁም የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ መክሯል፡፡
የፀጥታ ማሳሰሲያ መልዕክቶችን ከአሜሪካ ኤምባሲ ለማግኘት መመዝገብ የሚቻልበትን ሁኔታ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ባወጣው በዚህ የጉዞ ማስጠንቀቂያ ሠነድ መጨረሻ ላይ አስፍሯል፡፡ (ከሥር ከተቀመጠው የእንግሊዝኛው የማስጠንቀቂያ ሠነድ በታች ማግኘት ይቻላል፡፡)
ዜጎቹ ሠላማዊ ሰልፎችና ትላልቅ ስብሰባዎች ላይ እንዳይገኙ፣ አካባቢዎቻቸውን ያለመታከት እንዲያጠኑና የሚገኙበትን የግል ደኅንነት ሁኔታ እንደዲገመግሙም የማስጠንቀቂያ ሠነዱ መክሯል፡፡
መንግሥቱ ለሰልፎች ምላሽ ለመስጠት ኃይል ሊጠቀምና ቀጥታ ተኩስ ሊከፍትም እንደሚችልና ሰላማዊ ይሆናሉ የተባሉ ሰልፎችም ያለማስጠንቀቂያ የኃይል ብተና እርምጃ ሊወሰድባቸው ወይም ሰልፎቹ ወደ ሁከት ሊለወጡ እንደሚችሉ ዜጎቹ እንዲያስታውሱ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ አስጠንቅቋል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎች የደኅንነት ሁኔታቸውን እንዲከታተሉና በፍጥነት መውጣት ካለባቸውም ሊጠቀሙበት የሚችሉት አማራጭ ዕቅድ እንዲያዘጋጁም አሳስቧል፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ሠራተኞች ኦሮምያን፣ አማራን፣ ሶማሊን፣ ጋምቤላን፣ ደቡብ ኢትዮጵያን ክልሎችና የኢትዮጵያና የኬንያ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያና የኤርትራን የድንበር አካባቢዎች ጨምሮ ወደ ብዙ የሃገሪቱ ክፍሎች የግል ጉዞዎችን እንዳያደርጉ የተገደቡ መሆናቸውንም መግለጫው አመልክቶ ለሥራ የሚደረጉ ጉዞዎች በተናጠል እየታዩ እንደሚፈቀዱም ገልጿል፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ሠራተኞች ወደ አዲስ አበባና አዲስ አበባ ውስጥ ያለ ገደብ መጓዝና መንቀሳቀስ እንደሚችሉ የማስጠንቀቂያው ሠነድ ጠቁሟል፡፡
በአካባቢው ስላለው የአል-ሻባብ እንቅስቃሴ፣ የውንብድና ቡድኖች እና ሌሎችም የደኅንነት ሥጋቶች ኢትዮጵያን በሚመለከተው የመረጃ ምዕራፍ የደኅንነት ክፍሉን ሠነዶች እንዲያዩ መግለጫው መክሯል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የግንኙነት ሁኔታ ለመተንበይ አስቸጋሪ በመሆኑ ምክንያት የዩናይትድ ስቴትስ ዜጎች በስማርት ትራቭለር ኢንሮልመንት ፕሮግራም – ኤስ.ቲ.ኢ.ፒ. /ስቴፕ/ ከሚያደርጉት ምዝገባ በተጨማሪ በቴክስት ወይም ኤስኤምኤስ የደኅንነት መረጃ ማግኘት እንዲችሉ የሞባይል ስልክ ቁጥሮቻቸውን ለኤምባሲው እንዲያስመዘግቡ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ በጥብቅ አሳስቧል፡፡


ትግላችንን ከዳር ለማድረስ የሚከተሉትን 8 ተጨባጭ እርምጃዎች ሕዝባዊ ትግሉ በቀጣይነት ይወስዳል



ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
በሀገራችን ኢትዮጵያ የተከሰተው ስር የሰደደ የፖለቲካ ቀውስ በሰለጠነ የውይይትና የድርድር መንገድ እንዲፈታ ለሀገር ደህንነት ከሚያስቡ የአገር ሽማግሌዎችም ሆነ ከተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ወዳጆቹ ጭምር የቀረበለትንና የሚቀርብለትን ጥሪ አሌ ብሎ፤ ይህ እኩይ የጥቂት ሽፍቶች ሥርዓት ለ25 ዓመታት ሲያካሄድ የቆየውን የሕዝብና የሀገር ሀብት ዝርፊያ ከማቆም ይልቅ “ሀገሪቷን መዝረፍ ካልቻልኩ አቃጥያት እጠፋለሁ” ብሎ የመጨረሻው የሆነውን የጥፋት መንገድ ከሰሞኑ “የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ” በሚል ስያሜ ባወጀው “የባርነት አዋጅ” ለሁሉም ግልጽ አድርጓል። ይህንን የወያኔ የዘራፊዎች ቡድን ለረጅም ጊዜ በቅርብ ስንከታተልና በተግባርም ስንፈትነው ለቆየነው የነፃነት ኃይሎች ይህ እርምጃው ስንጠብቀውና ስንዘጋጅበት የነበረ ስለሆነ በእውነቱ በፍጹም አልገረመንም። ትንሽም ቢሆን ያስገረመን ይህንን የመጨረሻ ጥይቱን እንደዚህ በቶሎ መጠቀሙ ነው። የመጨረሻ ጥይቱ ነው የምንለው ከዚህ በኋላ ሊጠቀምበት የሚችለው ምንም ሌላ መሳሪያ እንደሌለው ስለምናውቅ ነው።
በእርግጥ በዚህ አዋጅ ውስጥ አገዛዙ ሊወስዳቸው ያሰባቸው እርምጃዎች አብዛኛዎቹ ከዚህ በፊትም እራሳቸው ካወጧቸው ህጎችና ህገመንግስቱም ውጪ ያለምንም ከልካይ ሲተገብሯቸው የነበሩ እርምጃዎች ናቸው። የመንግሥትን ስልጣን ከተቆጣጠሩ ጀምሮ በስልጣናቸው በመጣ ጉዳይ አንድም ጊዜ ሕጋቸውን አክብረው አያውቁም። ያለሕግ ሲያስሩ፤ ያለሕግ ሲገድሉ፤ ያለሕግ የመገናኛ ብዙሀንን ሲዘጉና ሲያፍኑ፤ ከሕግ ውጪ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶችን ሲያፈርሱና ያላፈረሱትን ደግሞ እራሳቸው የመረጡላቸውን መሪዎች ሲያስቀምጡ ነው እስካሁን የዘለቁት። ከዚህ አንጻር ይህ አዋጅ ቀድሞውንም ኢሕጋዊ የሆነ ስራቸውን ይበልጥ ኢሕጋዊ በሆነና አይን ባወጣ መንገድ፤ ለፈረንጆች ማባበያ ያጠለቁትን የሕጋዊነት ጭምብል አውልቀው እርቃናቸውን ከመታየታቸው ባሻገር ብዙ አዲስ ነገር የለውም። ይህን አዋጅ ከዚህ በፊት ሲያደርጉት ከነበረው በተለየ እንድንመለከተው የሚያደርገን ከአዋጁ እናገኝበታለን ብለው የሚያስቡትና በሕዝባችን ላይ ሊያሳርፉት የፈለጉት፤ ከተሳካላቸው ዘላቂ አንድምታ ያለው የተገዢነት ስነ ልቦና ውስጥ ሕዝቡ እንዲገባ የሚያደርጉት ሙከራ ላይ ነው።
ምንም በማያሻማ መልኩ ይህ አዋጅ ተግባራዊ እየሆነ ባለበት ሁኔታ ምንም አይነት የፖለቲካ መፍትሄ ሊኖርም ሊሞከርም የማይችል እንደሆነ ግልጽ ሆኗል። የህወሓት አገዛዝ ከጉልበት ውጭ ምንም ሌላ መንገድ የማያውቅ አጥፊ ኃይል እንደሆነ ለወዳጅም ለጠላትም ያሳወቀበት አዋጅ ነው። ይህን አዋጅ ሲያውጁ ሰው ሆኖ መኖርን የናፈቀውና ካሁን በኋላ ያለነፃነት በፍጹም አልኖርም ብሎ ፍርሀትን በሚገርም ጀግንነት አሸንፎ ውድ ሕይወቱን እየከፈለና እየታገለ ያለውን፤ ከሞላ ጎደል መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ፤ እንደገና በፍርሀት ቆፈን ውስጥ መልሼ ከትቼ ከቀድሞውም የባሰ ባርነት ውስጥ ዘፍቄ እገዛዋለሁ ብሎ አምኖ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ካሁን በኋላ ባርነትን የሚሸከምበት ምንም ጫንቃ የለውም። በዚህ በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሕዝብ በፍጹም በፍጹም ተመልሶ የባርነት ሕይወት ውስጥ ሊኖር አይፈቅድም። ስለዚህ ከዚህ በኋላ የፍትህና የነፃነት ኃይሎች ዋና ተግባር ያላቸውን አቅም ሁሉ አስተባብረውና ነፃነት የራበውንና የጠማውን ሕዝባቸውን ከጎናቸው አሰልፈው፤ ጊዜውና ሁኔታው የሚፈቅደውን ተለዋዋጭና ተለማጭ የትግል ስልት እየተጠቀሙ ይህ አዋጅ በፍጹም ተግባራዊ እንዳይሆንና እንዳይሳካ ማድረግ ነው። ይህን የባርነት አዋጅ ለማስፈጸም በመሪነትና በዋና አስፈጻሚነት የሚንቀሳቀሱት ኃይሎች፤ ይህ የባርነት አዋጅ በኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ እንዲተገበርና እንዲሳካ ለማድረግ የሚሞክሩ ወይንም ከዚህ ዘራፊ ሥርዓት ጋር በጥቅም ተሳስረው ከዚህ የባርነት አዋጅ ጋር የሚተባበሩ ማናቸውም ኃይሎች ሁሉ ከአሁን ጀምሮ የሕዝባዊ ትግሉ ቀንደኛ ዒላማዎች መሆናቸውን ግልጽ አድርጎ መንቀሳቀስ ይገባል። በዚህ ሕዝባዊ ትግል ላይ የሚሳተፉ የሕዝብ ወገኖችም ሆነ ይህንን ዘራፊ ሥርዓት የሚያግዙ ኃይሎች በደንብ እንዲረዱት የሚያስፈልገው ይህን አዋጅ አከሸፍነው ማለት የወያኔ ሥርዓት አከተመለት ማለት እንደሆነ ነው። ይህ አዋጅ ተሳካ ማለት ደግሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ ላልተወሰነ ጊዜ በባርነት መቀመቅ ውስጥ ሊኖር ተፈረደበት ማለት ነው። ለዚህ ነው አሁን የገባንበት ትግል የመጨረሻው የሞት ሽረት ትግል ነው የምንለው።
ለመሆኑ ይህ አዋጅ የሚደነግገው ምንድን ነው? ለምንድን ነው በፍጹም እንዲሳካ የማንፈቅድለት “የዘመናዊ ባርነት አዋጅ” ነው የምንለው?
“ባርነት” የሰውን ልጅ ሰው የሚያደርገውን መሠረታዊ ነጻነቱን ገፍፎ፤ ፈንጋዩ ከሚሰጠው ፈቃድ ውጭ በራሱ ምንም የሚወስነው ነገር እንዳይኖር ከልክሎ፤ ያለውን የጉልበትም ሆነ የማሰብ አቅሙን ሁሉ በባርነት ለሚያሳድረው ባለቤቱ ሀብት መፍጠርና አገልግሎት መስጠት ላይ ብቻ እንዲያውል የሚያደርግ ሥርዓት ነው። ባርያ የኔ የሚለው ንብረት የለውም፤ በገዛ ራሱ ሰውነትና አዕምሮ ላይ ሥልጣን የለውም። የሰው ልጅ እንዲህ ዓይነቱን ማንነቱን የሚነጥቅ በደል እሺ ብሎ በፈቃደኝነት አይቀበልም። ስለዚህ ይህን እንዲቀበል በጉልበት ማስገደድን ይጠይቃል። ይህን ለማድረግ ደግሞ ባርያ ፈንጋዮች የመጀመሪያ ሥራቸው ባርያ የሚያደርጉትን ሰው ከሰውነቱ የሚመነጨውን የነፃነትና ሰው የመሆን ፍላጎት በጉልበትና በሰቆቃ መንጠቅ ነው። አንዴ ይህን የውስጥ ማንነቱን ከነጠቁትና ባርያውን ወደ እንሰሳነት ከቀየሩት በኋላ እንደፈለጉት ለማድረግ በቀጣይነት ጉልበት መጠቀምም አያስፈልጋቸውም። በሕይወት የሚያቆየውን የሚበላውን መጥነው እየሰጡ እስከሚሞት ድረስ ጉልበቱን እየበዘበዙ ለራሳቸው ሀብት ማጋበስ ነው። ይህን በቀጣይነት ለማድረግ ባርያው ለራሱ ጥቅም እንዳያስብ መሆን አለበት። የሚያስበውን የሚነግሩት እነሱ፤ የሚሰማውን ወሬና ከማን ጋር መነጋገር እንዳለበት የሚወስኑለት እነሱ፤ የሚንቀሳቀስበትን ቦታ የሚወስኑለት እነሱ፤ መቼ መተኛትና መነሳት እንዳለበት የሚፈቅዱለት እነሱ፤ ምን ሥራ መሥራት እንዳለበት የሚፈቅዱት እነሱ፤ በሕይወት መኖርና አለመኖሩን የሚፈቅዱለት እነሱ፤ ባጠቃላይ ሕይወቱ በነሱ ፈቃድ ላይ የተመሰረተች እንጂ ከዚያ ውጭ ሕይወት እንደሌለው እንዲቀበል ማድረግ አለባቸው።
ይህን ለማድረግ ከሚጠቀሙት ጉልበት በተጨማሪም ሰውየው ይህ ኑሮው በግድ የተጫነበት ሳይሆን በተፈጥሮ ከፈጣሪው የተለገሰው እጣ ፈንታው እንደሆነ እንዲያምን ይጥራሉ። ይህን የሚያደርጉት ሰዎች በቁጥር ትንሽ ስለሆኑ በባርነት የሚኖሩት ሰዎች ተባብረው ከገቡበት የባርነት ቀንበር ራሳቸውን እንዳያላቅቁ ይህ የማይቻል እንዲሆን በባርያዎቹም መሀከል ልዩነት መፍጠርና አንዱ ባርያ ሌላውን የሚጠብቅበት መንገድ ማመቻቸትም አንዱ የመግዥያ መሣሪያቸው ነው። የተወሰኑትን ጥቂት ባርያዎች በአንጻራዊነት ቀለል ያለ የቤት ውስጥ ሥራ እያሠሩና ከሌሎች ባርያዎች በተለየ ከጌቶቻቸው የተረፈ ፍርፋሪ ምግብ እያበሉ እራሳቸውን እንደባርያ እንዳያዩና ሌላውን የመስክ ሥራ እየሠራ የሚፈጋውን ባርያ እየናቁና እንዳያምጽ የመቆጣጠር ሥራ ያሠሯቸዋል። ለሌላውም ባርያ “የጥሩ ባርያነት” አርአያ አድርገው ያቀርቧቸዋል። የሰው ልጅ እዚያ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ያገራችን ሰዎች አገሩን ላጣ ሰው እንሚተርቱት “ቢጭኑት አህያ ቢጋልቡት ፈረስ” የሆነ እንሰሳ ይሆናል ማለት ነው።
የወያኔ ጥቂት ዘራፊ መሪዎች ይህን አዋጅ ሲያውጁና በተግባር እናሳካዋለን ብለው ሲገምቱ በትግሉ ነጻነቱን እያወጀ ያለውን የኢትዮጵያን ሕዝብ እዚያ ባርነት ደረጃ ላይ እናደርሰዋለን ብለው ገምተው ነው። በዚህ አዋጅ ላይ እነሱ ከፈቀዱለት ሰው ውጭ ያለ ኢትዮጵያዊ ምን መናገር እንደሚችል፤ ምን ማሰብ እንደሚችል፤ ከማን ጋር እንደሚያወራ፤ ምን ዜና እንደሚሰማ፤ ምን ማንበብ እንዳለበት፤ የት የት ቦታ መንቀሳቀስ እንደሚችል፤ ምን ሥራ እንደሚሠራ፤ በስንት ሰዓት ከቤቱ ወጥቶ በስንት ሰዓት እቤቱ መግባት እንደሚችል፤ የራሱን ንብረት እንዴትና መቼ ማንቀሳቀስ እንደሚችልና ይህንን እነሱ ከፈቀዱለት ውጭ በራሱ ፍላጎትና ተነሳሽነት ምንም ዓይነት ነገር ቢያደርግ ሕይወቱን እስከመንጠቅ ድረስ የሚደርስ እርምጃ እንደሚወስዱበት በዚህ የዘመናዊ ባርነት አዋጃቸው አውጀዋል። በቃሊቲ፣ ቂሊንጦ፣ ዝዋይና ቁጥራቸው ተዘርዝሮ በማያልቅ የማጎርያና የማሰቃያ እስር ቤት ያሰሯቸውን ዜጎች ከንጋት 11 ሰዓት እስከ ቀን 11 ሰዓት ድረስ ውጭ ወጥተው ጸሀይ እንዲሞቁና እግራቸውን እንዲያፍታቱ ከመፍቀድ በቀር ቀሪውን ሰዓት በተቆለፈ ቤት ውስጥ እንዲቀመጡ እንደሚያደርጉት ሁሉ በዚህ አዋጅም በሀገሪቱ ድንበር 50 ኪሎ ሜትር ሬድየስ እና ከዋና ዋና መንገዶች በግራና በቀኝ 25 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚኖር ኢትዮጵያዊ ሁሉ (ይህ ባገሪቱ ያሉትን ሁሉንም ከተሞችና ትናንሽ መንደሮች ከሞላ ጎደል ያካልላል) ከምሽቱ 12 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12 ሰዓት ድረስ እራሱን በገዛ ቤቱ ውስጥ እንዲያስር የወሰነ እጅግ የሚገርምና በዛሬ ዘመን ሊታሰብ የማይችል የጅምላ እስር አዋጅ ነው። ይህ አዋጅ ከተሳካለት ማንም ኢትዮጵያዊ፤ ከነሱና ከቡችሎቻቸው በቀር፤ እራሱን ከጥቃት ለመከላከል የሚያስፈልገውን ማናቸውንም ዓይነት መሣሪያ እንዳይይዝ የሚከለክልና ያለውንም የሚቀማ ስለዚህም ለዘላለሙ በፍርሀትና በድንጋጤ እንዲኖር፤ በራስ የመተማመን ስሜቱን እንዲሰልብ ያለመ አዋጅ ነው። ይህ አዋጅ ከተሳካ እነሱ የኢትዮጵያውያንን ጉልበት እንደፈለጉ እየመዘበሩ የሚደልቡበት፤ ሌላው ኢትዮጵያዊ በገዛ ሀገሩ የበይ ተመልካች ብቻ ሳይሆን ጉልበቱንና የሀገሩን ሀብት ለነሱ እየገበረ የሚኖርበትን የዘመናዊ ባርነት ሥርዓት እንዲቀበል የሚያደርግ ነው። በዚህ ስድስት ወራት ውስጥ ይህንን ፍላጎታቸውን በኃይል ካሳኩ ከዚያ በኋላ አዋጁን ቢያነሱት እንኳን፤ ማሰሩንና መግደሉን ቢያቆሙት እንኳን፤ ይህ ቅስሙ የተሰበረ ሕዝብ ሰጥ ለጥ ብሎ ይገዛልናል ብለው አምነው የሚወስዱት እርምጃ መሆኑን ላንድ አፍታ እንኳም መዘንጋት የለበትም።
ለመሆኑ እንዲህ አይነት እርምጃ በዛሬው ዓለምና በዛሬይቱ ኢትዮጵያ ሊሠራ ይችላል ብለው እንዴት ገመቱ?
አሁን ያለውን የኢትዮጵያ ሕዝብ የደረሰበትን የነፃነት ፍላጎት ደረጃና ባጠቃላይ የዓለማችንን ሁኔታ በክፍት ልቦና ለሚመለከት ሰው በሀገራችን ያለውንና እነሱ ራሳቸው የፈጠሩትን የፖለቲካ ቀውስ በዚህ ዓይነት አዋጅ እንፈታዋለን ብለው ማሰባቸው በራሱ በነሱ በሞራ በተሸፈነ ትንሽ ጭንቅላት ውስጥ የሚርመሰመስ የራሳቸው የተለየ የቅዠት ዓለም ውስጥ የሚኖሩ፤ ይህ የቅዠት ዓለማቸው ግን ከእውነተኛው ዓለም እውነታ ጋር ሲጋጭባቸው የሚሠሩትን እስከማያውቁ ድረስ የሚምታታባቸው ግማሽ እብዶች መሆናቸውን ነው የሚገልፀው። በመጀመሪያ፣በዚህ አዋጅ አማካይነት እየታገሉት ያሉት ከማን ጋር እንደሆነ በፍጹም አላወቁም። በነሱ የቅዠት ዓለም፤ ትግላቸው ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ሳይሆን እነሱ “ጥቂት” ከሚሏቸው የነሱን “የልማትና የሕዳሴ ጉዞ” ከሚቃወሙ ወይንም ካልተዋጠላቸው ግለሰቦችና ድርጅቶች ጋር ነው። ከእነኝህ ጥቂት ግለሰቦችና ድርጅቶች ጋር ለሚደረግ ትግል ግን ለምን በመላው ሕዝብ ላይ ጦርነት ማወጅ እንዳስፈለጋቸው መቼም በትክክል በሚሰራ አዕምሮ ታስቦ የሚደረግ አይደለም። ከመላው ሕዝብ ጋር በሚደረግ ትግል ደግሞ እነኝህን እርምጃዎች በመውሰድ እናሸንፋለን ወይንም ያለሕዝብ ትብብር እነኝህን እርምጃዎች ተግባራዊ እናደርጋለን ብለው እንዴት ሊያምኑ እንደሚችሉ በሙሉ አዕምሮው ለሚያስብ ሰው ለመገመት አስቸጋሪ ነው። ሕዝቡ ቤቱ ውስጥ ያለው ቴሌቪዥን ላይ ምን እንደሚሰማ ለመቆጣጠር ቀደም ብሎ በሕዝቡ ትግል የፈረሰው “የአንድ ለአምስት” ጥርነፋ አሁንም ይሠራል
ስለዚህም ልጅ አባትና እናቱን፤ ወላጆች ደግሞ ልጆቻቸውን ይሰልሉልኛል ብለው በቅዠት ዓለማቸው ካላመኑ በስተቀር ዛሬ እውነታው በምድር ላይ የለም። ለመሆኑ፣ በሀገሩ ውስጥ ያለውን የሳተላይት መቀበያ ሳህን ሁሉ ከየቤቱ ጣርያ ላይ ለማውረድ የሚያስችል የሰው ኃይል አለን ብለው እንዴት ሊያምኑ ቻሉ? በየመንግሥት መሥሪያ ቤት ያለውና በግል ድርጅቶች ውስጥ የሚሠራውን ሠራተኛ ሁሉ “በሥራ መለገም ወንጀል ነው” ብለው ሲደነግጉ ይህንን እንዴት እናስፈጽማለን ብለው ገምተው ነው? ዳሽን ቢራና ፔፕሲ አልጠጣም፤ የህወሓት ንብረት በሆነው ሰላም አውቶብስ አልሄድም፤ ገንዘቤን በህወሓትና እሱን በሚያገለግሉ ባንኮች ውስጥ አላስቀምጥም፤ የመሶቦ ሲሚንቶን አልገዛም ብቻ ሳይሆን በባርነት ታስሬ የምኖርበትን ቤት ከናካቴው አልሰራም ብሎ ያመረረን ሕዝብ እንዴት አድርጎ ነው ፔፕሲንና ዳሽን ቢራን ሊግተው ያሰበው? እንደው እዚህ ግባ የማይባል ደሞዝ ከፍለው መሣሪያ ያስታጠቁት የወታደርና የፖሊስ ኃይል ለዚህች ደሞዙ ብሎ ራሱንና ወገኖቹን ለዘላለማዊ ባርነት ለመዳረግ የሚተጋ ግዑዝ ኃይል ነው ብሎ በዚህ በባዶ ትዕቢት በተወጠረ ንቀታቸው ቢያስቡ እንኳን፤ ይህ ቢበዛ ከ200ና 300ሺ በላይ የማይደርስ ኃይል፤ የሀገሪቱን ድንበር የመጠበቅ ሥራውን ሁሉ ትቶና ከድንበር ላይ ነቅሎ ለዚህ አዋጅ ማስፈጸሚያ ሥራ ቢያውለው እንኳን፤ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የተነሳንና እንዳስፈላጊነቱ በመሣሪያ ኃይል እራሱን ለመከላከል ያደራጀን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ሕዝብ እንዴት አድርጎ ያሸንፋል ብሎ ጤነኛ አዕምሮ ያለው ሰው ሊያምን ይችላል? ከዛሬ በኋላ እንኳንስ ሠራዊቱን በፍላጎት ለመልቀቅ እረፍት እንኳን መውስድ አትችልም ተብሎ በኃይል ተሰንጎ እንዲዋጋ የታወጀበት ሠራዊት ከሕዝቡ ጋር ጦርነት መግጠሙን ሲያውቅ አይደለም ከልቡ ሊዋጋና ሊያሸንፍ ከሕዝቡ ጋር ወግኖ መልሶ አዛዦቹንና ከሕዝብ ጋር የሚያዋጉትን የሀገርና የሕዝብ ጠላቶች ሊወጋ እንደሚዘጋጅ፤ ይህን እንኳን ማድረግ ቢያቅተው ከነመሣሪያው ጠፍቶ ሊሰወር እንደሚችል በትዕቢት የተወጠረና ማሰብ ያቆመ ጭንቅላት ካልሆነ በስተቀር በትክክል ለሚያስብ ሰው እንዴት ይሳነዋል? በመቶ ሺ እስኴር ኪሎ ሜትሮች በሚቆጠር አካባቢ የሚንቀሳቀስን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ሕዝብን የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ስንት ሚሊዮን ተባባሪዎቹን ተማምኖ ነው ሊቆጣጠረው የሚችለው? በሌላ አነጋገር የማሰብ ኃይላቸው ፍጹም ተመናምኖ ያለቀው የአገዛዙ መሪዎች እንኳን ይህንን አዋጅ ያለሕዝብ ትብብር እጃቸው ላይ ባለው ኃይል እናሳካዋለን ብለው ያምናሉ ለማለት በጣም አስቸጋሪ ነው። ሕዝቡ ደግሞ በዛሬ ዘመን በራሱ ላይ ባርነትን ለመጫን ይተባበራል ብሎ መገመት በፍጹም የሚቻል አይደለም።ይልቁንም ወያኔዎች የተማመኑበት የሚመስለው በተለመደ ባዶ ድንፋታቸው ሕዝቡን አስፈራርተው፤ ወይንም የተወሰኑ ሰዎችን ገድለውና አስረው በዚህ እርምጃቸው ሕዝቡ ከተሸማቀቀ በኋላ ለነጻነቱ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ያቆማል ብለው ነው እየቆመሩ ያሉት። የዚህ ክፉ ቁማር ውጤት ግን እነሱ የጠበቁት ሳይሆን እስካሁን ዘርፈው ያካበቱትን ንብረት ሳይበሉ ተሰባብረው የሚወድቁበትን፤ የኢትዮጵያ ሕዝብም በዚህ ዘረኛና ዘራፊ ሥርዓት መቃብር ላይ እውነተኛ ነጻነቱን የሚቀዳጅበት የመጨረሻው ሂደት እንደሚሆን አያጠራጥርም።
ይህ ግን ስለተመኘነው የሚመጣ ሳይሆን በሥራችንና በትግላችን እውን የምናደርገው ድላችን ነው የሚሆነው!
ታዲያ እዚያ የምንናፍቀው ድላችን ላይ ለመድረስ በሕዝባዊ ትግሉ የሚወሰዱ እርምጃዎችና ዋና ዋና ዒላማዎች ምንድን ናቸው?
ቀደም ብዬ እንዳልኩት የወያኔ መሪዎች ይህን በፍጹም ሊሳካ የማይችል እርምጃ መውሰዳቸው ሳይሆን የሚገርመው ይህንን የመጨረሻ የተስፋ መቁረጥ እርምጃቸውን እንዲህ በቶሎ መውሰዳቸው ነው የሚገርመው። እንዲህ ዓይነት ፍጹም ውጤቱን በቅጡ ያላሰቡበት እርምጃ ውስጥ የከተታቸው ደግሞ በዚህ ባጭር ጊዜ ሕዝባዊ ትግሉ የወሰዳቸው እርምጃዎች ከሚጠበቀው በላይና ባልተጠበቀ ፍጥነት ውጤታማ በመሆናቸው ነው። ባንድ በኩል በሀገር ውስጥ የሚደረገው የሕዝባዊ
እምቢተኝነት እንቅስቃሴ ባጭር ጊዜ ትግል የበሰሉ ወጣት አመራሮችን አፍርቶ በየጊዜው የሚቀያየሩና በምድር ላይ የሚፈጠሩ ሁኔታዎችን ከግምት እያስገባ የሚሄድ ተለዋዋጭ የትግል ስልቶችን በመጠቀም ሕዝቡን በሰፊው ያሳተፈ ቀጣይነት ያለው ትግል ማካሄድ በመቻላቸው ነው። ከዚህ ጋር ተያያዥነት ያለው ትልቁ ነገር ይህ ህዝባዊ እምቢተኛነት እንቅስቃሴ በአንድ የሀገሪቱ ክፍል ብቻ ሳይሆን በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል በፍጹም ባልተጠበቀና የወያኔን ዘረኛ መሪዎች ባስደነገጠ መልኩ በደል ባስተሳሰረው የአንድነት መንፈስ መካሄዱ ነው። የወያኔን ዘረኛ መሪዎች ብርክ ያስያዛቸው ጎንደር ላይ የአማራ ሕዝብ ተገልብጦ ወጥቶ ወያኔን ወጊድልኝ ከማለቱ ባሻገር የበቀለ ገርባን ምስል ይዞ “የኦሮሞ ደም ደማችን ነው” የሚል መፈክር እያሰማ መውጣቱና ከኦሮሞ ሕዝብ ትግል ጋር አጋርነቱን ማሳየቱ ነው። በኢሬቻ በዓል ላይ የኦሮሞ ወጣቶች “የአማራ በደል የኛም በደል” ነው ብለው በጎንደርና በጎጃም ለሚደረገው ትግል ወገንተኛነታቸውን ማሳየታቸው ነው። በሌላ በኩል ደግሞ በሁሉም ክልሎች ሕዝቡ ለሚያደርገው ሰላማዊና የሰለጠነ ትግል የወያኔ መሪዎች መልስ ጥይት መሆኑን በዓይኑ እየተመለከተ ሲሄድና በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ የትግል ጓዶቹን እየቀበረ ሲሄድ፤ አረመኔን በሰለጠነ ትግል ብቻ ማስቆም እንደማይችል አውቆ የሕዝባዊ እምቢተኝነት ትግሉን በሕዝባዊ አመጽ ለመደገፍ እየወሰደ ያለው ዝግጅትና መለስተኛ እርምጃዎች ናቸው።
ዛሬ በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች ለመሞት ብቻ ሳይሆን ለመግደልም የቆረጡ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ አርበኞች በረሀ የወጡበት ጊዜ ነው። ዛሬ የአርበኛ ታጋይ አበራ ጎባውን ዓይነት ጀግና ተዋጊዎችና አዋጊዎች ብዙ የአጋዚ ጦር ደምስሰው የሚሰዉ ብርቅዬ የኢትዮጵያ ልጆች ይህን ሥርዓት ከስሩ ለመመንገል የተዘጋጁበት ጊዜ ነው። እንዲህ ዓይነቶች ጀግኖች በኦሮሚያ የተለያዩ ቦታዎች፣ በአርባ ምንጭ፣ በቴፒ፣ በኮንሶ፣በጋምቤላ፣ በአፋር የጀንግንነት ተግባራትን ፈጽመው አሳይተውናል። ዛሬ የህወሓት አገዛዝ የሚመራው ጦር እየከዳ እንዲህ ዓይነት ጀግኖችን የሚቀላቀልበት ወቅት ነው። ዛሬ የብዙ ጊዜ እንቅስቃሴያችን ፍሬውን ለማፍራት የተዘጋጀበት፤ ትግሉን ከዳር ለማድረስ ሁኔታዎች የተመቻቹበት ጊዜ ነው። የወያኔ መሪዎች ይህንን ጠንቅቀው አውቀዋል። ለዚህ ነው ይህንን የመጨረሻ የተስፋ መቁረጥ እርምጃዎችን እየወሰዱ ያሉት።
ይህ በጥሩና በአመርቂ ሁኔታ እየተካሄደ ያለ ትግል ግን እመጨረሻው ምዕራፉ ላይ ሳይደርስ በፍጹም መቆም የለበትም። “የነብርን ጅራት አይይዙም፤ ከያዙም አይለቁ” የሚለው የአበው ብሂል እዚህ ላይ ይሠራል። ሕዝባዊ ትግሉን እዚህ ካደረስነው በኋላ ከዳር ሳናደርሰው መመለስ ከቶ አይቻለንም። ማድረግ ያሉብን ነገሮች ደግሞ ግልጽ ናቸው። አሁን በመላ አገራችን የተቀጣጠለው ሕዝባዊ ትግል እስካሁን ከነበረው በላይ አጠናክሮ መቀጠልና አዲስ ለተፈጠረው ሁኔታ የሚመጥኑ አዳዲስ እርምጃዎችን መውሰድ ይገባል። የትግል ዒላማዎቻችንን ከዚህ በፊት ከነበሩት በተጨማሪ ይህንን የባርነት አዋጅ ለመተግበር የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ላይ ሁሉ ማነጣጠር ይኖርበታል። ከዚህ አንፃር ይህንን የባርነት አዋጅ ለማክሸፍና ትግላችንን ከዳር ለማድረስ የሚከተሉትን ተጨባጭ እርምጃዎች ሕዝባዊ ትግሉ በቀጣይነት ይወስዳል፤
1. ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ነፃነትን የሚሻ ሁሉ ከሚመስለው ጋር ይደራጅ ስንል ቆይተናል፤ አሁን ከመደራጀትም አልፎ ራሱን ለመከላከል ከዚያም አልፎ ለሚደርስበት ጥቃት ተመጣጣኝ ምላሽ ለመስጠት ይዘጋጅ። ባርነትን በጉልበት ሊጭንብን ጦር ሰብቆ የመጣውን እኩይ ኃይል፤ ምርጫችን ሆኖ ሳይሆን በላያችን ላይ የተጫነ ግዴታ ስለሆነ ከእንግዲህ ገድሎ መሞት እንጂ “በሰላምተኝነት” መሞት የለም። ራስንና ሕዝብን ከህወሓት ሽብር ለመከላከል በየቦታው የተደራጁና የታጠቁ ህዝባዊ ቡድኖች አሉ፤ ተጨማሪ ቡድኖችም በከፍተኛ ፍጥነት እየተደራጁ ነው፤ ። ነፃነት የጠማው ኢትዮጵያዊ ሁሉ እነዚህን ቡድኖች ይደግፍ፣ ይቀላቀል።
2. ይህ ትግል የኢትዮጵያውያን ሁሉ ትግል ነው። የተደራጁ ቡድኖች ትግል ብቻ አይደለም። በቡድን ብቻ ሳይሆን በግልም ጭምር ለህወሓት አመፃ የአመፃ ምላሽ ለመስጠት ሁሉም ነጻነት ፈላጊ ኢትዮጵያዊ መዘጋጀት አለበት። የወያኔን ፋሽስታዊ ስርዓት ከበላይ ሆነው የሚዘውሩት ብቻ ሳይሆን በመካከለኛና በስር ሀላፊነት የሚሰሩ የፌደራል ፖሊስ፤ የየከተማው የፖሊስ አባላት፤ ለወያኔ የስለላ ተቋማት የሚሰሩ ሰራተኞች፤ የመከላከያ ሹማምንት፤ በተለያዩ ደረጃ ላይ ያሉ የህወሀት/ኢህአዴግ ካድሬዎችን ስም ዝርዝር፤ የስራ ሀላፊነት፤ የመኖሪያና የስራ አድራሻ እንዲሁም ስልክና የኢሜል አድራሻቸውን የያዘ ሙሉ መረጃ አለን። በየቀበሌው የሚሰሩ ትናንሽ የስርዓቱ አገልጋዮችን የያካባቢው ነዋሪዎች ያውቋቸዋል። ይህ የባርነት አዋጅ እስካልተቀለበሰ ድረስ ይህን አዋጅ ለመተግበር የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ሁሉ የህዝባዊ ትግሉ የቡድንም ሆነ የግል ኢላማዎች ናቸውና ጊዜው ሲደርስ ይህን መረጃ ለህዝባችን በይፋ የምንገልጽ መሆናችን እንዲታወቅ እንፈልጋለን።
3. ይህ የባርነት አዋጅና የአዋጁ ባለቤት ህወሓት/ኢህአዴግ በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ መንገዶች “መሠረተ – ልማቶች” ሳይሆኑ መሠረተ – ጥፋቶች ናቸው፤ አውራ ጎዳናዎች አስጠቂዎቻችን ናቸው። በእነዚህ መንገዶች እየተጓጓዘ ነው የአጋዚ ጦር ወገኖቻችንን እየፈጀ ያለው። ስለሆነም ለትግላችን የሚያስፈልጉ ካልሆኑ በስተቀር መንገዶችን መዝጋት ተቀባይነት ያለው ሥራ ነው፤ ከነፃነታችን የሚበልጥ አንዳች ቁሳዊ ሀብት የለም።
4. የታወቁ የሥርዓቱ ቀንደኛ አራማጆች ብቻ ሳይሆኑ ይህንን የባርነት አዋጅ ለማስፈፀም የሚሯሯጡ ግለሰቦች፣ ቡድኖችና ተቋማት ሁሉ ጠላቶቻችን ናቸው። እነዚህ ሁሉ የትግላችን ዒላማዎች ናቸው። በየሠፈሩ አዋጁን የሚያስፈጽሙ ስማቸው ተለይቶ ይፋ ይደረጋል፤ የነፃነት ኃይሎች በእነዚህ ኃይሎች ላይ በቡድንም በግልም እርምጃ ይወስዳሉ።
5. የጦርና የፓሊስ ሠራዊት አባላት በተለይም የአጋዚ ጦር አባላት – ይህ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለእናንተ ገደብየለሽ ሥልጣን የሰጠ በመሆኑ የምትጠቀሙ አይምሰላችሁ። እናንተ ዜጎችን በመግደላችሁ፣በማሰራችሁና በማሰቃየታችሁ የሚጠቀሙት አለቆቻችሁ ጄኔራሎች እና የህወሓት/ኢህአዴግ ሹማምንት ናቸው።አዋጁ ከሌላው ሕዝብ ያላነሰ እናንተንም ባርያ የሚያደርግ ነው፤ የዓመት እረፍት እንኳን መውሰድ እንዳትችሉ የተገደባችሁ መሆኑን እወቁ። በአዋጁ ተፈፃሚነት ለእናንተ የሚተርፋችሁ የእድሜ ልክ ፀፀትና ከሕዝብ ጋር የምትገቡበት ቁርሾ ነው።የእናቶችና የሕፃናት ዋይታና ለቅሶ ይሰማችሁ፤ህወሓት/ኢህአዴግ እናንተን ተጠቅሞ የኢትዮጵያን ሕዝብ በባርነት እየገዛ መሆኑ ይታያችሁ።ከኢህአዴድ መወገድ በኋላ የሚመጣው ሥርዓት እናንተን የሚጠቅም እንጂ የሚጎዳ አለመሆኑን አውቃችሁ ከአገዛዙ ጋር ያላችሁን ግኑኝነት በጥሱ።ዛሬውኑ ወስኑ ! በወገኖቻችሁ ላይላለመተኮስ ለራሳችሁ ቃል ግቡ !!! የመሣሪያዎቻችሁን አፈሙዝ በሙስና ወደደለቡት አለቆቻችሁ አዙሩ፤አልያም ሥርዓቱን ከድታችሁ የነፃነትኃይሎችን ተቀላቀሉ። ሥርዓቱን ለሚከዱ የሠራዊቱ አባላት ሕዝባዊ ትግሉ የክብር አቀባበል እንደሚያደርግ ቃል ይገባላችኋል፤ በየቦታውም ይህን የሚያስተባብሩ አካላት ተደራጅተዋል። ይህን ዕድል ከመጠቀም ይልቅ ሥርዓቱን ለማቆየት የወሰናችሁ የሠራዊቱ አባላት የምትዋጉት የጠላት ጦርን ሳይሆን የራሳችሁን ሕዝብ መሆኑን እወቁ። በምንም ዓይነት ሕዝብን ማሸነፍ አትችሉም።
6. የጦርና ፓሊስ ሠራዊት አባላት ቤተሰቦችና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በሠራዊቱ ላይ ጫና ያሳድር።ሠራዊቱ ከኢትዮጵያ አብራክ የወጣ ነውና የኢትዮጵያ ሕዝብን ይሰማል።የኢትዮጵያ ሕዝብ ለህወሓት/ኢህአዴግ ሹማምንት ድሎት ሲባል በገዛ ልጆቹ መገደልና መረገጥ የለበትም። ሠራዊቱ የህወሓት/ኢህአዴግ ሠራዊት መሆኑ እንዲያበቃ ሁለገብ ጥረት እናደርጋለን።
7. በአገዛዙ የስለላ መዋቅሮች የምትሠሩ ወገኖቻችን ኃላፊነት አለባችሁ። ማንን እየተከላከላችሁ፤ ማንን እያጠቃችሁ እንደሆነ አስተውሉ። ለራሳችሁ ደህንነት እና ለህሊናችሁ የሚበጃችሁ ከሕዝብ ጎን መቆም ነውና ዛሬውኑ ወስኑ፤ እናንተም ወደ ሕዝብ ትግል ስትመጡ ለመቀበል ዝግጁ ነን፤ ይህን እድል አታስመልጡ። በተመሳሳይም የኢህአዴግ አባላት ጎራችሁን ለዩ። አምርሮ ለዘመተብን ጠላት የመረረ ምላሽ ለመስጠት ተዘጋጅተናል።
8. ህወሓት/ኢህአዴግ ከመነሻው ጀምሮ በአርሶ አደሩ እየነገደ ያለ እኩይ ኃይል ነው። ዛሬ የመንግሥትን ሥልጣን የያዙት ኃይሎች አርሶ አደሩ እየተራበና እየታረዘ ጠግቦ የሚያድር አስመስሎ ለዓለም የሚናገሩ ውሸታሞች ናቸው። ከዚህም በተጨማሪ መሬትን እየቀሙ ለራሳቸውና ለወዳጆቻቸው የሚያድሉ በልተው፣ ገፈው፣በዝብዘው የማይጠረቁ ሆዳሞች ናቸው። ከእንግዲህ የኢትዮጵያ አርሶ አደር በባርነት ለሚገዛው አገዛዝ ግብር፣ መዋጮ፣ የምርጥዘርም ሆነ የማዳበሪያ እዳ አይከፍልም፤ ካድሬዎች በሚጠሩት ስብሰባ አይወጣም፤ ራሱ በመረጣቸው የአገር የቀበሌና የገበሬ ማህበራት አስተዳዳሪዎች እንጂ በሥርዓቱ ካድሬዎች አይተዳደርም፤ ለዳኝነት ወደ አገዛዙ ፍርድ ቤት አይሄድም። በያካባቢው የራሱን ዳኞች ከመሀሉ መርጦ ይዳኛል እንጂ!
9. በማናቸውም የመንግሥት ሥራ ላይ የተሠማራ የመንግሥት ሠራተኛ ሥራውን በአግባቡ ሠራ ማለት ይህንን የባርነት አዋጅ አስፈፃሚ ሆነ ማለት እንደሆነ ይወቅ። እያንዳንዱ ነፃነቱን የሚወድ የመንግሥት ተቀጣሪ የዕለት ተዕለት ሥራውን ሲፈጽም የሥራው ውጤት ህወሓት/ኢህአዴግን የሚያዳክም እንጂ የሚያጠናክር እንዳልሆነ እርግጠኛ ይሁን። ሕዝባዊ እምቢተኝነትና ሕዝባዊ አሻጥር በሁሉም ቦታዎችና በሁሉም የሥራ ዓይነቶች ተግባራዊ ይሆናሉ። በባርያ ፈንጋይ ላይ አሻጥር መፈፀም በምድር የሚያስመሰግን በሰማይም የሚያፀድቅ ተግባር እንደሆነ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ያውቃል፤ በጣሊያን ፋሽስት የወረራ ዘመን የመንግሥት ሠራተኞች የነበሩ የውስጥ አበርኞች አብነቶቻችን ናቸው። ሕዝባዊ አሻጥር በኢትዮጵያ በህወሓት አገዛዝ ሥር ያለ የመንግሥት ሠራተኛ የሥራ ባህል ይሆናል።
10. ኢትዮጵያውያን በአገራችን በነፃነት መኖር የምንችለው ይህን የባርነት አዋጅ በማክሸፍ የህወሓት/አገዛዝን አስወግደን የሕዝብ ይሁንታ ያለው መንግሥት ስንመሠርት ብቻ እንደሆነ እያንዳንዱ ወጣት ይወቅ። ሕዝባዊ እምቢተኝነት፣ ሕዝባዊ አመጽና ሕዝባዊ አሻጥር የወጣቱ ትውልድ ባህል ይሆናሉ። ከእንግዲህ የወጣቱ ሙሉ አካላዊና አዕምሮዓዊ ጉልበት ይህንን አዋጅ በማክሸፍ ሥራ ላይ ይውላል። በየቦታውና ጊዜው ተስማሚ የሆነ የትግል ስልት በመቀየስ የዚህን አስከፊ ሥርዓት ፍፃሜ ለማፍጠን የተለያዩ አደረጃጀቾችን በሥራ ላይ አውለናል። ወጣቶች የራሳቸው ፈጠራና አካባቢያዊ ግብዓቶችን በመጠቀም የህወሓት አገዛዝን በኃይል ለመከላከል የሚያደርጉትን ጥረት እንደግፋለን፤ እናበረታታለን።
11. በየአካባቢው አካባቢያዊ ጥያቄዎች ሊኖሩን ይችላሉ፤ አካባቢያዊ ጥያቄዎችን ለትግል ማንሳት የሚበረታታ ነው፤ ያም ሆኖ ግን ትግላችን የሚደጋገፍና ወደ ጋራ ድል የሚያመራ እንዲሆን የተቻለንን ሁሉ ጥረት እናደርጋለን። በተለያዩ ማኅበረሰቦችና በተለያዩ እምነት ተከተያዮች መካከል የተፈጠረውን መግባባትና መተጋገዝ ለማዳበር ጠንክረን እንሠራለን። አገራዊ ኅብረት ለመፍጠር ቀንና ሌሊት እንተጋለን።
12. በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንም ሙሉ ጉልበታቸውና ኃይላቸውን የህወሓት አገዛዝን ማዳከም ብቻ ሳይሆን ማጥፋት ላይ እንዲያተኩሩ እንሠራለን። በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የባርነት አዋጅ ታውጆበታልና በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንም ምላሽ የመረረ ይሆናል።
ውድ ወገኖቼ!ee992-asee
በመጨረሻ ማሳሰብ የምሻው አንድ ወሳኝ ነጥብ አለ። ይህ የህወሓት ዘራፊ ቡድን በአንድ በኩልና በዋናነት ይህንን የባርነት አዋጁን በጉልበት ለማስፈጸም ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እያደረገ ነው፤ በሌላ በኩል ደግሞ ሰላም የሚፈልግ ለማስመሰል እሱ ከመረጣቸውና ባፈና መዋቅሩ ውስጥ ከቦ እያስፈራራ ካስቀመጣቸውና በተግባር ሽባ ካደረጋቸው የፖለቲካ ሰዎች ጋር እደራደራለሁ የሚል የተለመደ ማደናገሪያውን ለማስኬድ እየሞከረ እንደሆነ እያየን ነው።ይህ አካሄድ አውቀው ሊታለሉ የሚፈልጉ ፈረንጆችን ያታልልበት እንደሆነ እንጂ በሀገሪቱ ያለውን የፖለቲካ ቀውስ በፍጹም ሊፈታ እንደማይችል የታወቀ ነው። የፖለቲካ ኃይሎች በነፃነት መንቀሳቀስና እንወክለዋለን ከሚሉት ሕዝብ ጋር በነፃነት መምከር ሳይችሉ ትርጉም ያለው ወደ ዘላቂ ሰላም የሚወስድ ድርድር ማድረግ ከቶውኑም አይችሉም። ሽጉጥ በግንባርህ ላይ ደግኖ “ከነብስህ ወይንም ከገንዘብህ” ብሎ ምርጫ ለሚሰጥህ ማጅራት መቺ ሕይወትህን ለማትረፍ “ገንዘቤን ውሰድ” ብትለው በማጅራት መቺውና በሰለባው መካከል “የሰጥቶ መቀበል ድርድር ተደረገ” እንደማይባል ሁሉ በግንባራቸው ላይ ሽጉጥ ደግኖ፤ ወይንም በእስር ቤት ከከተተ በኋላ የሚደረግ ድርድር በምንም አይነት በነፃነትና በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ድርድር ተደርጎ አይወሰድም፤ ተቀባይነትም የለውም። ስለዚህ ይህ አዋጅ በተግባር ላይ እስካለ ድረስ የሀገር ውስጥ ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን በማስፈራራት እየሰበሰቡ ወያኔን ብቻ አሸናፊ የሚያደርግ የድርድር ሙከራ ከእስረኞች ጋር የሚደረግ ድርድር ስለሆነ ምንም ተቀባይነት የለውም። የሕዝባዊ ትግሉም በእንዲህ አይነት የማደናገሪያ ሂደት ከጀመረው የነፃነት ትግል ላንዲት ጋት እንኳን እንደማይዘናጋ እንዲታወቅ ያስፈልጋል።
ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ!!!!
በዚህ የመጨረሻ የፍልሚያ ወቅት ጥቂቶቻችን ልናልፍ እንችላለን። ለነፃነታችን ስንል ሕይወታችንን ብንሰጥ ፈጣሪያችን በአምሳሉ ሲፈጥረን የሰጠንን የሰውነት ማንነት እውን ለማድረግ በምናደርገው ትግል ነውና የምናልፈው፤ የፈጣሪያችንን ፈቃድ ለማስፈጸም የገበርነው ሕይወታችን ነውና በደስታ የምንጠጣው ጽዋችን ነው። ይልቅስ ፈጣሪያችን ለምንግዜውም ይቅር የማይለን ከሌላው እንሰሳ ለይቶ የሰጠንን ይህን በነፃነት የታጀበ የሰው ልጅነት፤ እንደ እንሰሳ ለሚበላና ለሚጠጣ ቁሳዊ ጥቅም ሸጠን፤ ሰው መሆንን በእንሰሳዊ የባርነት ሕይወት ቀይረን እኛ ባርነትን ተቀብለን ከራሳችን አልፎ ባርነትን ለልጆቻችን ያስተላለፍን እንደሆነ ነው። የዛሬ ትውልድ ኢትዮጵያውያን የባርነትን ኑሮ ከኛ እንዳያልፍና ወደ ልጆቻችን እንዳይጋባ ማስቆም ታሪክ የጣለብንና በእርግጠኛነት የምንፈጽመው ተግባራችን እንደሆነ ከቶውንም አልጠራጠርም።
እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ
አንድነት ኃይል ነው !!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!
ጥቅምት 7 ቀን 2009 ዓ.ም.

Saturday, October 22, 2016

ሰበር ዜና በሱማሌያ የሚገኘዉ የህወሃት ሰራዊት በአል ሸባብ ተመታ።


በሶማሌያ በኑር ፋህን መንደር አካባቢ ሲንቀሳቀስ የነበረ የወያኔ የመከላከያ ሰራዊት በአልሸባብ ቀለበት ዉስጥ በመግባቱ ድንገተኛና ያልተገመተ ጥቃት ደርሶበታል በዚህ ድንገተኛ ጥቃት 11 ኢትዮጵያዊያን ወታደሮች ሲገደሉ 3ቱ በከፍተኛ ሁኔታ መጎዳታቸዉን ትናንት ከስፍራዉ የደረሰን መረጃ ሲያመለክት።
ይህንን የልሸባብ ጥቃቱን ተንተርሶ የሶማሌ ደህንነት ሚኒስቴር አብዱረዛቅ መሃመድ አህመድ ወደ ስፍራዉ የሶማሌ ወታደሮች እንዲንቀሳቀሱ ቀደም ብለዉ ወደ አካባቢዉ የመከላከያ አዛዦች ጥያቄ ማቅረባቸዉን ከስፍራዉ የወጣ መረጃ ጠቁሟል።
ህወሃት በኢትዮጵያ ላይ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ ከደነገገ ወዲህ ኮማንድ ፖስቱን ወይም ተወርዋሪን በማጠናከር ያጋጠመዉን የሐይል እጥረት ለማስተካከል ከሶማሌያ ወታደሮችን ወደ ሐገር ቤት ካሸጋገረ በኋላ አልሸባብ በኢትዮጵያ ወታደሮች ላይ የፈጸመዉ ይህ ጥቃት ነገሮችን የተወሳሰቡ አድርጓቸዋል።
በመሆኑም ከኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ዉስጥ መረጃ የሰጠን ወንድማችን እንዳስቀመጠዉ ከአሚሶም የአፍሪካ ህብረቱ ጦር ዉስጥ በማፈንገጥ ወደ ኬንያ ሁለት የኢትዮጵያ ወታደሮች ያፈነገጡ ሲሆን በኮረኔል አይኖም መስፍን የሚመራ አሳሽ ቡድን ባዶ እጁን በመመለሱ ምክንያት በሶማሌያ የሚገኘዉ የህወሃት ወታደሮች ላይ የህብረቱ ጦር ያለዉን እምነት እያጣ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል።።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )

ሰበር መረጃ… የህወሃት ኮማንድ ፖስት (ተወርዋሪ) ሐይል እክል ገጥሞታል።


ይህ አዋጅ በአማራዉ ክልል እና በኦሮሚያ ክልል ላይ ብቻ ተግባራዊ እንዲሆን ከማዘዙ በላይ ለስርአቱ የሚያገለግሉ የልዩ ሐይል የመከላከያ የፌደራልና የአየር ሐይል አባላት ባጠቃላይ ለተሰማሩበት ግዳጅ ተግባራዊ ምላሽ እየሰጡ አይደለም ሲል የወታደራዊ ኮማንድ ፖስት ተወርዋሪ ግዜያዊ ደህንነቱ ለጀኔራል ሲራጅ ፈርጌሳ መልእክት መላኩን የዉስጥ ሰዎቻችን አስታዉቀዋል።
የአማራና የኦሮሞ ኢትዮጵያዊያን ወታደሮች አዋጁ የትግራይን ክልል አይነካም! የትግራይን ህዝብ ደህነት እንድንጠብቅ በብርቱ ታዘናል! በየትኛዉም ክልል ላይ የሚንቀሳቀሱ የትግራይ ልጆችን ኮማንድ ፖስት ወይም ተወርዋሪዉ እንድንጠብቅ ታዘናል! ለምን ?
ለምሳሌ በአብዛኛዉ በሐገሪቷ ዉስጥ የአስቸኳይ ግዜ አዋጁ ከታወጀ ጀምሮ ከታሰሩ ኢትዮጵያዊያን መካከል አንድም ትግሬ የለም ከተገደሉ መካከልም አንድም ትግሬ የለም በተለይም እንዲታደኑና እንዲወገዱ እንዲሁም እንዲታሰሩ ማዘዣ ከጣባቸዉ ዉስጥ አንድም ትግራይ የሉበትም! ለምን ?
ሰራዊቱ አሻፈረኝ በማለት እየጸና ነዉ ” መብት የተከበረለትና መብቱ የተጣሰ ሁለት ህዝብ በአንድ ሐገር ላይ እየተመለከትን ለመብት ጣሺዎች ህጋዊ ወንጀል አንፈጽምም ” በሐገሪቱ ብሐራዊ ደህነት ላይ የመጨረሻ ከፍተኛ ክፈተት ተፈትሯል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )

ከአማራ ክልል የተወከሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተቃወሙ


ተወካዮቹ አዋጁ አፋኝ በመሆኑ በክልላችን እንዲሰራ አንፈቅድም በማለት ተቃውሞአቸውን ገልጸዋል። ተወካዮቹ የያዙትን አቋም እንዲለውጡ ከትናንት ጀምሮ በደህንነቶች ሲዋከቡ ውለዋል። ተቃውሞአቸውን ለመግለጽም የተዘጋጀላቸውን ምግብ ሳይመገቡ ቀርተዋል።
ይህ አፋኝ ህግ በክልላችን ህዝብ ላይ ተግባራዊ እንዲሆንና ከህዝብ ጋር እንድንጣላ አንፈልግም ያሉት ተወካዮቹ፣ አዋጁ እንዳይጸድቅ በጽኑ ተከራክረዋል። 137 የሚሆኑት የምክር ቤት አባላት በአንድ ድምጽ ያሳዩት ተቃውሞ ያልተጠበቀ ሲሆን፣ ትናንትና ዛሬ ከሌሎች አባላት ጋር ሳይገናኙ ለብቻቸው ተገልለው ውለዋል። “ህዝብ ሲረገጥና ሲሞት ዝም ብለን አናይም፣ የመረጠን ህዝብ የእሱን መብት ልናስጠብቅለት እንጅ በአዋጅ ልናስገድለው አይደለም” በማለት ጠንካራ አቋም መያዛቸው የአገዛዙን ከፍተኛ ሹሞች አስደንግጧል። የገዢው ፓርቲ ልሳናት ግን አዋጁ በሙሉ ድምጽ እንደጸደቀ ገልጸዋል።
አዋጁ ይፋ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ አገዛዙ በሙሉ ወታደራዊ ሃይሉ በመንቀሳቀስ በርካታ ዜጎችን ወደ እስር ቤት ወስዷል። በአንዳንድ ወረዳዎች ከ 1 ሺ በላይ ዜጎች ታስረው እንደሚገኙ የሚደርሱን መረጃዎች የሚያመለክቱ ሲሆን፣ ኮማንድ ፖስት የተባለው አዲሱ ወታደራዊ ገዢ ሃይል ባለፉት 3 ቀናት 1 ሺ 600 ሰዎች ብቻ መታሰራቸውን ገልጿል። ይሁን እንጅ ባለፉት 3 ቀናት በ10 ሺ ዎች የሚቆጠሩ ዜጎች መታሰራቸውን የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።
በኦሮምያ ክልል የኮማንድ ፖስት አባላት ሴቶችን እየደፈሩ እንዲሁም ዝርፊያ እየፈጸሙ መሆኑን የሚናገሩት ነዋሪዎች፣ ለፖሊስ ሲያመለክቱ ለ6 ወር ያክል ምንም ስልጣን ስለማይኖረን ምንም ማድረግ አንችልም የሚል መልስ እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል። በአማራ ክልል ኮማንድ ፖስቱ የጦር መሳሪያ ለመቀማት እንቅስቃሴ በጀመረበት ወቅት ከአንዳንድ አርሶአደሮች ተቃውሞ ደርሶባቸዋል።
በጭልጋ ወረዳ ሻሀርዳ ቀበሌ ጥቅምት 14/2016 ዓም ቸሩ መንክር የተባለውን ጎልማሳ ከቤቱ ወደ ስራ ሲሄድ ገድለው ጠመንጃውን ወስደዋል ። የግለሰቡ የቀብር ስነስርዓት በማግስቱን ሸኸዲ አካባቢ የሚገኝ ማህበረ ስላሴ ገዳም ተፈፀሟል ። ጥቅምት 19፣ 2016 ደግሞ ጭልጋ ወረዳ ሻሃርዳ ቀበሌ እያዩ ተረፈ የሚባል ጎልማሳ ቤት ወታደሮቹ በምሸት ሰአት ቤቱን ሰብረው በመግባት ገለው መሳሪያውን ወሰደዋል። እያዩ በአካባቢው ህዝብ ዘነድ ከፍተኛ ከበሬታ እንደነበረው ምንጮች ገልጸዋል። በዚሁ ቀን አናጋው የተባለውን ሰው ግደለው መሳሪያውን ወስደውታል። የአካባቢውን ህዝብ ስለአንድነት በመስበክ የሚታወቅ እንደነበር የሚገለጹት የአካባቢው ምንጮች፣ የቀብር ስነስርዓቱም ዛሬ ይፈጸማል።
የኮማንድ ፖስት አባላት ነን የሚሉ ሰዎች ኢሳትንና ኦ ኤም ኤንን ታያላችሁ ያሉዋቸውን ሰዎች እየያዙ ማሰር የጀመሩ ሲሆን፣ በበርካታ ከተሞች ህዝቡ ዲሾችን እንዲያወርድ እያስፈራሩ ነው። ይሁን እንጅ ህዝቡ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም አሁንም ኢሳትንና ሌሎች የመገናኛ ብዙሃንን መመልከቱን ቀጥሎአል። በአንዳንድ አካባቢዎች ደግሞ ህዝቡ ዲሽ አናወርድም በማለት በእምቢተኝነቱ እንደ ጸና ነው።
በሌላ በኩል ጎንደር ከተማ ውስጥ ታሰረው የነበሩ በርካታ ወጣቶች ከ5 እስከ 100 ሺ ብር የዋስትና ገንዘብ እያስያዙ እንዲወጡ ፍርድ ቤት ውሳኔ አስተላልፏል። ብዙዎቹ ወጣቶች መንገድ ላይ የታፈሱ ሲሆን፣ ምንም ወንጀል ሊገኝባቸው ባይችልም ገንዘብ አምጡና ውጡ መባላቸውን ምንጮች ገልጸዋል።

Monday, October 17, 2016

Prof Berhanu Nega message October 17, 2016

ሰበር_መረጃ….አስቸኳይ የፋይናንስ አዋጅ ሊታወጅ እንደሆነ ተሰማ። የብሔራዊ ባንክ ውጭ ምንዛሪ ካዝና ባዶ ነው

የኢህአዴግ ጽ/ቤት በትርምስና የእርስ በእርስ ውንጀላ ላይ ነው። በውጪ እና በሀገር ውስጥ ኢንቬስተሮች ከኤክስፖርት ይገኝ የነበረው የውጭ ምንዛሪ በ5 ወራት ውስጥ በ71.1 በመቶ በመቀነሱ ለመጀመሪያ ጊዜ የ1.9 ቢሊዮን ዶላር የገቢ ውድቀት ታይቷል። ከተጠበቀው በታች በመቀነሱ ይሄንን የህዝብ አገልግሎት ሰጪ የሆኑ የትምህርት ቤት በጀት (የመምህራን ደሞዝን ጨምሮ)፣ የጤና አገልግሎት፣ ትራንስፖርት፣ ከፍተና ወጪ ያስከተለው የፖሊስ ሰራዊትና የወታደሮች ደሞዝ በዚህ የበጀት ቀውስ ምክንያት በመስተጓጎሉ አዲስ አዋጅ ማስፈለጉ ተሰምቷል።
ከሁሉም አስከፊ የሆነው ከቻይና ሌሎች አበዳሪዎች ለኢንቨስትመንስት ጉዳይ ተብሎ የተገኘው ብድር 16 ቢሊዮን ዶላር በመድረሱ በመጀመሪያው የክፍያ በ2016 አመት አስከፊ የፋይናንስ ቀውስ መገባቱ ምክንያት ሆኗል። ኢትዮጵያ በአሳሳቢ የዕዳ ሽክም ከአለም 11ኛ ሆናለች። ከዚህ ባለፈ ለውድቀቱ ተጨማሪ ምክንያት የሆነው እርዳታ ሰጪ ሀገሮች በየጊዜው የሚያስገኙት የበጀት ድጋፍ እየቀነሰ በመምጣትና ወደ ሰብዓዊ አስቸኳይ የምግብ ርዳታ ላይ ትኩረት በማድረጋቸው መሆኑም ጭምር ነው።
Image result for comerica bank of ethiopia

የአርበኞች ግንቦት7 መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።

” ከዚህ በኋላ የፍትህና የነፃነት ኃይሎች ዋና ተግባር ያላቸውን አቅም ሁሉ አስተባብረውና ነፃነት የራበውንና የጠማውን ሕዝባቸውን ከጎናቸው አሰልፈው፤ ጊዜውና ሁኔታው የሚፈቅደውን ተለዋዋጭና ተለማጭ የትግል ስልት እየተጠቀሙ ይህ አዋጅ በፍጹም ተግባራዊ እንዳይሆንና እንዳይሳካ ማድረግ ነው። ይህን የባርነት አዋጅ ለማስፈጸም በመሪነትና በዋና አስፈጻሚነት የሚንቀሳቀሱት ኃይሎች፤ ይህ የባርነት አዋጅ በኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ እንዲተገበርና እንዲሳካ ለማድረግ የሚሞክሩ ወይንም ከዚህ ዘራፊ ሥርዓት ጋር በጥቅም ተሳስረው ከዚህ የባርነት አዋጅ ጋር የሚተባበሩ ማናቸውም ኃይሎች ሁሉ ከአሁን ጀምሮ የሕዝባዊ ትግሉ ቀንደኛ ዒላማዎች መሆናቸውን ግልጽ አድርጎ መንቀሳቀስ ይገባል። በዚህ ሕዝባዊ ትግል ላይ የሚሳተፉ የሕዝብ ወገኖችም ሆነ ይህንን ዘራፊ ሥርዓት የሚያግዙ ኃይሎች በደንብ እንዲረዱት የሚያስፈልገው ይህን አዋጅ አከሸፍነው ማለት የወያኔ ሥርዓት አከተመለት ማለት እንደሆነ ነው። ይህ አዋጅ ተሳካ ማለት ደግሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ ላልተወሰነ ጊዜ በባርነት መቀመቅ ውስጥ ሊኖር ተፈረደበት ማለት ነው። ለዚህ ነው አሁን የገባንበት ትግል የመጨረሻው የሞት ሽረት ትግል ነው የምንለው።”
“በዚህ የመጨረሻ የፍልሚያ ወቅት ጥቂቶቻችን ልናልፍ እንችላለን። ለነፃነታችን ስንል ሕይወታችንን ብንሰጥ ፈጣሪያችን በአምሳሉ ሲፈጥረን የሰጠንን የሰውነት ማንነት እውን ለማድረግ በምናደርገው ትግል ነውና የምናልፈው፤ የፈጣሪያችንን ፈቃድ ለማስፈጸም የገበርነው ሕይወታችን ነውና በደስታ የምንጠጣው ጽዋችን ነው። ይልቅስ ፈጣሪያችን ለምንግዜውም ይቅር የማይለን ከሌላው እንሰሳ ለይቶ የሰጠንን ይህን በነፃነት የታጀበ የሰው ልጅነት፤ እንደ እንሰሳ ለሚበላና ለሚጠጣ ቁሳዊ ጥቅም ሸጠን፤ ሰው መሆንን በእንሰሳዊ የባርነት ሕይወት ቀይረን እኛ ባርነትን ተቀብለን ከራሳችን አልፎ ባርነትን ለልጆቻችን ያስተላለፍን እንደሆነ ነው። የዛሬ ትውልድ ኢትዮጵያውያን የባርነትን ኑሮ ከኛ እንዳያልፍና ወደ ልጆቻችን እንዳይጋባ ማስቆም ታሪክ የጣለብንና በእርግጠኛነት የምንፈጽመው ተግባራችን እንደሆነ ከቶውንም አልጠራጠርም።”ee992-asee

Sunday, October 9, 2016

የጀርመኗ ቻንስለር በአንድ ፓርቲ ቁጥጥር ሥር በዋለ ፓርላማ ንግግር አያደርጉም ተባለ

በሚቀጥለው ሳምንት ወደ አዲስ አበባ የሚመጡት የጀርመኗ መራሒተ መንግሥት (ቻንስለር) አንገላ መርከል በአንድ ፓርቲ ቁጥጥር ሥር በዋለ ፓርላማ ንግግር አያደርጉም ተባለ፡፡ ምንም እንኳን መንግሥት ቻንስለሯን በፓርላማ ተገኝተው ንግግር እንዲያደርጉ ቢጠይቅም፣ መርከል ግን ‹‹በአንድ ፓርቲ ቁጥጥር ሥር በዋለ ፓርላማ ውስጥ ንግግር ማድረግ ምንም ለውጥ አያመጣም፤›› በማለት ግብዣውን እንዳልተቀበሉት ለማወቅ ተችሏል፡፡
ቻንስለሯ ከእሑድ ጀምሮ ሦስት የአፍሪካ አገሮች የሚጐበኙ ሲሆን፣ በመጀመሪያ ወደ ማሊና ኒጀር ተጉዘው ኢትዮጵያ ሲመጡ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር ይገናኛሉ፡፡ በተጨማሪም የአፍሪካ ኅብረትን ይጐበኛሉ ተብሏል፡፡ ቻንስለሯ አዲስ አበባ ሰኞ አመሻሽ ላይ እንደሚደርሱ፣ አብሯቸውም የጀርመን ፌዴራል ጽሕፈት ቤት ባልረደቦች ብቻ እንደሚመጡ ተገልጿል፡፡ ከቻንስለሯ ጋር ምንም ዓይነት የቢዝነስ ልዑካን የማይመጣ ሲሆን፣ ይህም በሎጂስቲክስ ችግር መሆኑ ታውቋል፡፡ ቻንስለሯ ሰኞ አመሻሽ ላይ ከገቡ በኋላ ማክሰኞ በብሔራዊ ቤተ መንግሥት አቀባበል የሚደረግላቸው ሲሆን፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ጋር ረቡዕ ይገናኛሉ፡፡
ምንጮች ለሪፖርተር፣ ‹‹ቻንስለር መርከል በአገሪቱ በተፈጠረው ተቃውሞ የፀጥታ ኃይሎች ዜጐች ላይ እየወሰዱት ስላለው አላስፈላጊና ከመጠን ያለፈ ኃይል ከመንግሥት ጋር ይወያያሉ፤›› ከዚህም ባለፈ፣ ‹‹በቁጥጥር ሥር በተከፈተ›› የአገሪቱ የፖለቲካ ምኅዳር ላይ ይወያያሉ ብለዋል፡፡ ቻንስለሯ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር በሚኖራቸው ውይይት ስደተኞችን በተመለከተና ሽብርተኝነትን በመዋጋት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ይነጋገራሉ ተብሏል፡፡
ቻንስለሯ መርከል በአዲስ አበባ ቆይታቸው ወቅት፣ ከተመረጡ የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችና የሲቪል ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር ውይይት ያደርጋሉ፡፡ እንደ ምንጮች ገለጻ፣ ቻንስለሯ ስድስት ከሚሆኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችና የሲቪል ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር በጀርመን ኤምባሲ ይወያያሉ፡፡ ሆኖም የውይይቱ አጀንዳንና ተሳታፊዎቹ ማን እንደሆኑ ምንጮች ከመግለጽ ተቆጥበዋል፡፡
በቅርብ ጊዜያት ወደ ኢትዮጵያ ከመጡ የአገር መሪዎች በተለየ ቻንስለሯ የተቃዋሚ ፓርቲዎች መሪዎችን ያነጋግራሉ ተብሏል፡፡ በቅርብ ዓመታት የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ፣ የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ፣ የደቡብ ኮሪያዋ ፕሬዚዳንት ፓርክ ጉዊን ሃይና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔትኒያሁ ከተቃዋሚዎች ጋር አለመገናኘታቸው ይታወሳል፡፡
ቻንስለሯ በአፍሪካ ኅብረት ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኘውን አዲሱን የጁሊየስ ኔሬሬ የሰላምና ደኅንነት ሕንፃ ማክሰኞ የሚመርቁ ሲሆን፣ በኅብረቱ አዳራሽም ንግግር ያደርጋሉ ተብሏል፡፡ ከኅብረቱ ሊቀመንበርንና ከሌሎች የኅብረቱ አመራሮች ጋር ይወያያሉ ተብሎም ይጠበቃል፡፡ አዲሱ የሰላምና ደኅንነት ሕንፃ እንዲገነባ የገንዘብ ድጋፍ ያደረገው የጀርመን ፌዴራል የውጭ ጉዳይ ሲሆን፣ ሕንፃው የተገነባውም በጂአይዜድ ነው፡፡

Wednesday, October 5, 2016

በኦሮሚያ ከተቀጣጣለው ህዝባዊ አመጽ ጋር በተያያዘ ዛሬ አንዲት አሜሪካዊት ተገደሉ።

የኢሬቻውን ዕልቂት ተከትሎ በኦሮሚያ ከተቀጣጣለው ህዝባዊ አመጽ ጋር በተያያዘ ዛሬ አንዲት አሜሪካዊት ተገደሉ። በአዲስ አበባ ፖሊስና ፌደራል ሃይል 24ሰዓት በተጠንቀቅ እንዲሆን ታዘዙ።
An American citizen was killed on Tuesday as a van carrying her and eight other foreigners came under attack as they were heading to a meeting.
Hospital sources say a stone thrown by unidentified assailants went through the back window of the van hitting the deceased, Sharon Ray, on the head.
The source from the Landmark Hospital in Addis Ababa also
said the van came under attack in Holeta, 26 miles from the capital Addis Ababa.
The source also said the United States Embassy in Addis Ababa has been notified of the incident.
Another lady who has sustained minor injuries was also treated at the Hospital and later released.
It is not clear if the attack is linked to the protest on Tuesday in the localities surrounding Addis Ababa. Residents in towns near the capital have staged protest rallies on Tuesday to denounce the killing of hundreds of festival goers in Bishoftu on Sunday at an annual cultural celebration by the Oromos.
Hundreds of ethnic Oromos and Amharas have been killed this year by security forces while protesting against the tyrannical regime in Ethiopia.

Tuesday, October 4, 2016

በአዲስ አበባ ትግሉ ከታሰበዉ በላይ ከቁጥጥር ዉጭ እየሆነ ነዉ::


አዲስ አበባ ለቀጣዩ ህዝባዊ ስርአት ቄጠማ እየጎዘጎዘች ለበሰበሰዉ ዘሰኛ የአሸባሪ ቡድን ህወአትም እሳት ለኩሳለች:: ከህወአታዊያን ወጭ ሁሉም በአንድነት አዲስ አበባ የገዳዮች መቀመጫ ላይ ተነስቷል:: ተኩስ በመላዉ አዲስ አበባ እየተሰማ ነዉ:: ሁሉም ነገር ቆሟል የጥይትና የአምቡላንስ ድምፅ ብቻ ነዉ የሚደመጠዉ::
ህዝቡ መንገዶችን ሁሉ እየዘጋ የወያኔ ንብረቶችን በማዉደም ላይ ነዉ:: ተናግረን ነበር ህዝብን አትናቁ ብለን:: ዉርድ ለራስ ብለን::
አመራር የተባለ ህወአታዊ የተባለ ሁሉ መግቢያ መዉጫ አጥቷል:: ሁሉም በእግሩ ወደየመኖሪያዉ እየተሯሯጠ ነዉ::
አዎ የግፈኞች መጨረሻ የከፋ ነዉ ብለን መክረን ነበር:: መጨረሻችሁ እየከፋ ነዉ:: ለህዝብስ ያዉም ለኛ ሞት አብሮን ኖሯል::
የተጎዱ የተገደሉም እንዳሉ መረጃዎች እየመጡ ነዉ:: እስካሁን አራት ስዎች በአንድ አካባቢ ብቻ ተገለዋል::
ከብስራተ ገብርኤል ቶታል 3 ቁጥር ማዞሪያ ጀምሮ ዘነብወርቅ፣ አየር ጤና፣ አለምባንክ፣ አለም ገና ባሉ አካባቢዎች ከትላልቅ ሆቴሎች ጀምሮ ሁሉም የንግድ ድርጅቶች ተዘግተዋል፡፡ ወጣቶች ተቃውሞውን እያስፋፉ ከአየር ጤና ጋር ለማገናኘት ጥረት እያደረጉ ነው፡፡ ተቃውሞውን ለመቀላቀል ሁሉም በንቃት እየተጠባበቀ ነው፡፡

ጥብቅ መረጃ . የእሬቻ ድብቅ ሴራ


በቅርቡ 29/9/2016 ከደብረ ዘይት የተነሱ 3 የጦር ጀቶች በአዳማ በኩል በማድረግ ለ33 ደቂቃዎች መሰወራቸዉንና ጉዳዩ በከፍተኛ ሚስጥር እንዲያዝ መረጃ አቀብዬህ እንደነበረ ታስታዉሳለህ። በመሆኑም ትናንት በሰጠሁህ ፍንጭ መሰረት ሁለት የበረራ ክፍል ሰራተኞች መረጃ ያወጣሉ ተብለው ተወስደዋል፤ እኔም ይህንን የማቀብልህ በፍጹም ድፍረት ነዉ፤ አብራሪዎቹ ከደብረ ዘይት የአየር ሐይል ጣቢያ በመነሳት የእሬቻ በአል በሚከበርበት የቢሾፍቱ አካባቢ ዝቅ ብለዉ በመብረርር የሙከራ ግዜ እንዲወስዱ መመሪያ እንደተላለፈላቸዉ ለማወቅ ችያለዉ፡ አብራሪዎቹ በመመሪያዉ መሰርት ዝግጅት ላይ እንዳሉ የመርዝ ጭስ ( የአድማ መበተኛ በሚል ) ሽፋን ለአስፈላጊ ጥንቃቄ መጠቀም ሊቻል ስለሚችል አዲስ የሆኑ ማስወንጨፊያዎችን እንዲለማመዱ እንዲሁም በጣም ዝቅ ብለዉ ለመብረር አካባቢዉ ላይ የልምምድ አጭር ቅኝት እንዲወስዱ ትእዛዝ ወጣ በዚህ ሁኔታ ላይ 3ቱም አብራሪዎች በአንድ ሐሳብ ተስማምተዉ ልምምዱን ጀመሩ! ነገር ግን በበረራ ወቅት ላይ ለ33 ደቂቃ ድምጽእቸዉን አጥፍተዋል የተባሉት አብራሪዎች ከአየር ሐይሉ ከፍተኛ አመራር ጋር ድርድር በማድረግ በዚህ አደገኛ በሆነ ግዳጅ ላይ መሳተፍ እንደማይፈልጉ ግዳጁ አደገኛ መሆኑንና ህዝብ ላይ ይህንን ተግባር እንደማይፈጽሙ ቢናገሩም የአየር ሐይሉ አመራሮች ከወያኔ ሰዎች በተላለፈዉ ትእዛዝ መሰረት አመጽ ካልተነሳ በስተቀር አፋኝ የሆነዉን ጭስ እንደማይጠቀሙ ይነግሩዋቸዋልነገር ግን አብራሪዎቹ የጦር ጀቶቹ በእንደዚህ ያለ ባሕላዊ ክብረት ላይ ዝቅ ብለዉ መብረራቸዉ በራሱ ከፍተኛ ወንጀል ነዉ፡በፍሹም አናደርገዉም ይህን የማትቀበሉን ከሆነ ጀቶቹን የራስችን ወሳኔ እንፈጽምባቸዋለን በማለት አሻፈርኝ ይላሉ! ነገሩ አጣብቂኝ ዉስጥ የከተታቸዉ የአየር ሐይሉ አመራሮች አብራሪዎቹ በሰጡት ዋስትና መሰረት በመደራደር ተስማምተዉ ወደ ምድር ኢንዲወርዱ ተደርገዋል! ዉድ ወዳጄ ይህንን ግዳጅ ሊወጣ የሚችል የአየር ሐይል አብራሪ ይኖራል የሚል እምነት የተመናመምነባቸዉ ጨካኞች የማስበርገግና የማሳደድ የመርዝ ጭስ የመጠቀሙን እንዲሁም በመትረየሶች የማጥቃትን የጦር ወንጀል ግዳጅ ወደ የጦር ሄሊኮፍተሮች እና ታንኮች በማዞር ከየት እንደመጡ በምይታወቁ ፊታቸዉን በሸፈኑ ግለሰቦች አየር ሐይል ዉስጥ ልምምድ ሲያደርጉ ቆይተዉ የግድያ እርምጃዉን በእሬቻ በል ላይ ወስደዋል፤ ይህንን መልእክት ለመላዉ ኢትዮጵያዊ አድርስልኝ ከእንግዲህ አንገናኝም፤ ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
( ጉድሽ ወያኔ )Image result for ethiopian air force