Sunday, April 23, 2017

የአሜሪካ ኮንግረስ ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ሕጎች ረቂቆችን እያወጣ ነው


hqdefault
በዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት ኢትዮጵያን በተመለከተ የሚቀርቡ የውሣኔ ሀሳቦችን «በተሳካ ሁኔታ አምክኛለሁ» ሲል የኢትዮጵያ መንግሥት ቢናገርም ኢትዮጵያን የሚመለከቱ ህጎች አሁንም በኮንግረሱ እየረቀቁ መሆናቸውን የህዝብ ተወካዮች አመልክተዋል።
የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ወርቅነህ ገበየሁ በመጋቢት መጨረሻ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ሁለት ረቂቅ ህጎችን እንዳጨናገፈ የሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
የኮንግረሱ የአፍሪካ ንዑስ ኮሚቴ ሊቀመንበር ለዝግጅት ክፍላችን በሰጡት ማብራሪያ «ኮንግረስ በምርጫ ሲቀየር ህጎች እንዳዲስ ለውሳኔ ይቀርባሉ እንጂ የተጨናገፈም ሆነ እንዲዘገይ የተደረገ ህግ የለም» ብለዋል።
ሙሉው ዘገባ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ።

ኦፌኮ’ ህልውናው ሊያከትም ነው ፤ የምርጫ ቦርዱ ፕሮፌሰር በቃና ታሪካዊ ውሳኔ ይጠበቃል


በኦሮሚያ ሰፊ ድጋፍ ያለው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ ኦፌኮ ህልውናውን ጠብቆ የመቆየት እድል እንደሌለው ለምርጫ ቦርድና ለስርዓቱ ቅርበት ያላቸው የኦህዴድ ሰዎች ለዛጎል ገለጹ። እንደ ገለጻው ኦፌኮ እንደ ፓርቲ እንዲቆይ የማይፈለገው በሁለት አበይት ምክንያቶች ነው።
የመጀመሪያው ከኦነግ በሁዋላ ኢህአዴግን የፈተነው ኦፌኮ በመሆኑና ሰፊ ድጋፍ ስላለው በዚህ መልኩ ሕዝብ የሚደግፈው ድርጅት በተለይ ኦሮሚያ ላይ እንዲኖር ስለማይፈለግ ነው። ሁለተኛው ምክንያት ቀጣዩን ምርጫ ኦሮሚያ ላይ ማሸነፍ ስለማይቻል ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት ለማድረግ በሚል እንደሆነ የመረጃው ባለቤቶች ያስረዳሉ። በሌላም በኩል ከድርድር የወጣው መድረክም ኦፌኮን ካጣ ባዶ እንደሚሆን በማሰብም ጭምር ነው ሲሉ ያክላሉ።
ኢህአዴግ ያቋቋመውንና በቀደሞው የምርጫ ቦርድ ሹም የሚመራው የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ያቀረበውን ሪፖርት ያስታውሱት ክፍሎች፤ በሪፖርቱ ከተወነጀሉት ሶስት ፓርቲዎች መካከል ኦፌኮ አንዱ መሆኑን ይታወሳል። ሰማያዊ ፓርቲና የጌዲዮ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት እና ኦፌኮ በኦሮሚያና በአማራ ክልል የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ “እንዲቀሰቀስና እንዲባባስ አድርገዋል” በሚል የቀረበውን ሪፖርት ሸንጎው አጽድቆ ፓርቲዎች እንዲከሰሱ ወሳኔ አስተላልፎ እንደነበር የሚታወስ ነው።
ለገለልተኛ አጣሪዎችና ለተባበሩት መንግስታት መርማሪዎች በሩን የዘጋው ኢህአዴግ፣ ሕዝባዊ አመጹን ተከትሎ ለጠፋው የሰው ህይውት ነጻና ገለልተኛ አጣሪዎች ምርመራ እንዳያደርጉ ሲከለክል ምክንያት አቅርቦ ነበር። ምክንያቱም ” ሉአላዊነትን የማስደፈር ያህል ነው” የሚል ነበር። ኢህአዴግ ይህንን ቢልም በአገሪቱ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ተጥሶባቸዋል የሚባሉ አካባቢዎችን ለጋዜጠኞች፣ ለለጋሽ አካላትና ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ለምልከታ ሲከለክል ይህ የመጀመሪያው እንዳልሆነ የሚገልጹ አሉ።
የዜናው ሰዎች እንደሚሉት ኢህአዴግ የሚፈራው ከውጪ ያሉ ተቃዋሚዎችን አይደለም። የአንድ ከፍተኛ ባለስልጣን ስም በመጥራት እነዚሁ ክፍሎች እንደተናገሩት ኢህአዴግ አገር ቤት ተነስቶ የነበረው ተቃውሞ አይነት ቀውስ በድጋሚ እንዳይፈጠር “የተኛውንም ርቀት” ይሄዳል። ከተፈጠረም በየትኛውም ወቅትና ሰዓት የወታደራዊ መንግስት ለማወጅና አገሪቱን “በይፋ” በወታደራዊ ስር ለማሰተዳደር ዝግጁ ነው።
በዚሁ መነሻ በኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን በአብዛኛው የአገሪቱ ሕዝብ ተቀባይነት ያላቸውን የኦፌኮን መሪዎችና ራሱን ፓርቲውን አግዶ ህልውናውን ማክሰም ሆን ተብሎ ሲሰራበት የነበረ ጉዳይ ነው። ይህንኑ እቅድ ተግባራዊ ለማደረግ ደግሞ ” ህግ” የሚባለውን ማደናገሪያ መጠቀም ግድ በመሆኑ ገለልተኛ እንዳልሆነ በየተኛውም የህብረተሰብ ክፍል የሚታወቀውን የ” ኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ጉባኤ” ሪፖርት መጠበቅ ግድ ነበር። ዜናውን የጠቆሙት የኦህዴድ ሰዎች ” ክስ እንዲመሰረት የተወሰነባቸው ፓርቲዎች ሲከሰሱ በጥቅሉ ምን እንደሚወሰንባቸው ባይታወቅም ኦፌኮ ግን እንደሚታገድና፣ የምርጫ ቦርድ የእውቅና ማስረጃን እንደሚነጠቅ፤ በዛውም እንደሚከስም፣ ሌላ ሕዝብ የሚያምናቸው ድርጅቶች እስኪበቅሉ ምርጫውም ያልፋል ” ብለዋል።
ዶክተር መረራ ጉዲና፣ በቀለ ገርባ ፣ ያለተዘመረለት ኦልባና ሌሊሳ እና በርካታ አመራሮቹን፣ አባላቱን፣ ደጋፊዎቹ እስር ላይ ያሉት ኦፌኮ መጪው ዕድሉ እንደተባለው መክሰም ከሆነ ይህንን ወሳኔ የሚወስኑት ፕሮፌሰር በቃና – የምርጫ ቦርድ “ዋና ሃላፊ” መሆናቸው ታሪኩን፣ አጋጣሚውን፣ እንዲሁም ውሳኔውን ልዩ እንደሚያደርገው ከኦህዴድ ሰዎች የተገኘው ዜና ያስረዳል።
የሰብአዊ መብት ኮሚሽኑንን ሪፖርት በተለያየ መልኩ ከመዘገብ ውጪ በኦፊሳል የተጠቀሱት ፓርቲዎች ላይ ምን ዓይነት እርምጃ እንደሚወሰድ የተባለ ነገር የለም። ይሁንና ተጠያቂ እንዲደረጉ መወሰኑ የዜናውን ተአማኒነት ያጎላዋል የሚል እምነት አለ። ኦፌዴን ሰማያዊ ፓርቲና የጌዲዮ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት የተወሰነባቸውን ውሳኔ አስመልክቶ የሰጡት ” በገለልተኛ ወገን ያልቀረበ ሪፖርት ተቀባይነት የለውም” ሲሉ መመለሳቸው አይዘነጋም።

የዶ/ር መረራ ፓርቲ ቀደም ሲል ስሙ ተነጥቆ ለአቶ ቶለሳ ቢሰጥም በአጭር ጊዜ ውስጥ ክርክሩን አቁመው ኦፌኮን ማቋቋማቸው አይዘነጋም። ኢህአዴግ የሚወዳደረው ፓርቲ ሲፈጠር ስሙን መንጠቅና ለሌላ አሳልፎ የምስጠት፣ አመራሮቹን አስሮ የማዳከም ለዩ ባህሪው እንደሆነ በስፋት የሚከሰስበት ጉዳይ ነው። አሁን በድርድር ላይ ያሉትን ፓርቲዎች ታሪክ ማየትም ይህንኑ ሃቅ ያጎላዋል።88c6732c

Friday, April 21, 2017

የአርበኞች ግንቦት7 አባላት የሆኑ ታጋዮች በደምቢያ ወረዳ ሰረባ መስኖ አጠገብ ሌሊት ላይ ጥቃት ፈጽመው


2 ገልባጭ መኪኖችና አንድ እስካቫተር መኪና የተቃጠሉ ሲሆን፣ በታጋዮች እና ድርጅቱን በሚጠብቁት መካከል ለ30 ደቂቃ ያክል የተኩስ ልውውጥ መካሄዱንና አንድ ወታደር መገደሉን ድርጅቱ ለኢሳት በላከው መረጃ አስታውቋል።
ኢሳት ወደ አካባቢው ነዋሪዎች ስልክ በመደወል በመኪኖች ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን ሲያረጋግጥ፣ በሰው ህይወት ላይ ስለደረሰው ጉዳት ግን ማረጋገጫ ሊያገኝ አልቻለም። የአይን እማኞች ጉራምባ ቀበሌ ላይ በተለይም በቀበሌው ሊቀመንበር አቶ መንግስቱ መኖሪያ ቤት አካባቢ ከፍተኛ የተኩስ ለውውጥ መካሄዱን ገልጸዋል።
አካባቢው በወታደሮች ቁጥጥር ስር በመውደቁ የተቃጠሉትን መኪኖች ብዛት በትክክል ለማወቅ እንዳልቻሉ፣ ነገር ግን 3 መኪኖች ጠዋት ላይ ተቃጥለው ማየታቸውን ተናግረዋል።
ወደ አካባቢው የተንቀሳቀሱት ወታደሮች የአካባቢው ሚሊሺያ እርምጃ ባለመውሰዱ መሳሪያቸውን እየቀሙ እያሰሩዋቸው ነው። በሌላ በኩል ትናንት ምሽት በጎንደር ከተማ ተጨማሪ የቦንብ ጥቃት የተፈጸመ ሲሆን፣ አንድ ታጣቂ ግለሰብ ጥቃቱን ባደረሱት ሃይሎች ተመትቶ ጉዳት ደርሶበታል፡፡
ጥቃቱ በቀጠናው የህወሃት ወኪል በመሆን የደህንነት ስራ ይሰራል በተባለው በአቶ አማረ አምባየ ላይ ያነጣጠረ እንደነበር ለኢሳት የደረሰው መረጃ ያሳያል። ግለሰቡ እና ጠባቂው ጉዳት ደርሶባቸው ለህክምና ወደ አዲስ አበባ መላካቸውንም መረጃው አክሎ አመልክቷል።
ጥቃቱን ተከትሎ ከሙሴ ባምብ ወታደራዊ ካምፕ የተንቀሳቀሰ አንድ ኦራል መኪና ከምሽት 5 ሰአት አካባቢ ልዩ ስሙ የኢትዮጵያ ካርታ በሚባለው ስፍራ ላይ በጥይት ተመትቶ ሲገለበጥ 4 ወታደሮች ወዲያውኑ ህይወታቸው ሲያልፍ፣ 5 ወታደሮች ደግሞ ቆስለዋል።
መኪናው ዛሬ ተጎትቶ ጎንደር አዘዞ ወደሚገኘው ወታደራዊ ካምፕ ተወስዷል። የቆሰሉ ወታደሮችም አዘዞ በሚገኘው የጦር ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ሲሆን፣ ሟች ወታደሮችም አዘዞ ሎዛ ማሪያም ቤ/ክርስቲን ተቀብረዋል፡፡
የአሁኑ ጥቃት በአንድ ሳምንት ጉዜ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ መፈጸሙ ነው። በሰራባ የመስኖ ፕሮጀክት አካባቢ ተደጋጋሚ ጥቃቶች የተፈጸሙ ሲሆን፣ ጥቃቱን በሚያደርሱ ታጋዮች ላይ እስካሁንም ምንም ጉዳት አልደረሰባቸውም።
ገዢው ፓርቲ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አማካኝነት ማንኛውንም አይነት የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተቆጣጥሬዋለሁ ቢልም፣ አሁንም በሰሜን ጎንደር የተለያዩ ወረዳዎች ጥቃቶች እየተፈጸሙ ነው።

ጎንደር አስረኛውን የቦንብ ፍንዳታ ትናት አስተናገደች


በጎንደር ከተማ በቀበሌ 15 ቀጠና 1 ፋሲለደስ እስታዲየም አካባቢ ነዋሪ የሆነው የሆነው የህውሀት የሰሜን ጎንደር ፣ የደቡብ ጎንደር ፣ የምእራብ ጎጃም የአካባቢው ማለትም የቀጠናው የህውሀት ሰብሳቢ ሊቀምንበር እና የትግራይ ልማት ማህበር ሊቀመንበር የሆነው አምባየ አማረ በተባለው ግለሰብ ሚያዚያ 12 ቀን 2009 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡47 ሰዓት ሲሆን መኖሪያ ቤቱ በቦምብ ጥቃት ተፈፅሞበታል ፡፡
ይህ በንዲህ እንዳለ በትላንትናው እለት በጎንደር የተፈጠረውን ችግር ለማረጋጋት ከሙሴ ባምብ ወታደራዊ ካምፕ ወታደር ጭኖ የተንቀሳቀሰ አንድ ኦራል መኪና ምሽት 4፡40 ላይ ልዩ ስሙ የኢትዮጵያ ካርታ የሚባለው ቦታ ላይ በጥይት ተመትቶ መኪናው ሲገለበጥ 4 ወታደሮች ወዲያውኑ ሲሞቱ 5 ቀላል ቁስለኛ ሆነዋ ኦራል መኪናው ዛሬ 13/08/2009 ከቀኑ 5 ፡ 00 ሰዓት ተጎትቶ ወደ ጎንደር አዘዞ ወደሚገኘው ወታደራዊ ካምፕ የመጣ ሲሆን የቆሰሉ ወታደሮች አዘዞ በሚገኘው የጦሩ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛሉ ሟቾችም አዘዞ ሎዛ ማሪያም ቤ/ክርስቲን ተቀብረዋል፡፡