የሚከተለው ጋዜጠኛ ሙሉቀን ተስፋው ከስፍራው ደዉሎ ካጠናከረው ዘገባ የተወሰደ ነው። የጎንደር ህዝብ ሰላማዊነቱን ያለፈው እሁድ ሐምሌ 24 አሳይቶ ነበር። ሆኖም እነዚህ ጋኔኖች ህዝቡን ከማክበር ህዝቡ እየሰደቡ፣ በህዝቡ ላይ በሚቆጣጠሪት ሜዲያዛቻ እየሰነዘሩ፣ ንቀት ያለበት የጥጋብ ንግግር እየተናገሩ አካባቢው እንዲታመስ አይደረጉት ነው። የሙሉቀንን ዘገባ እንሆ
ጎንደር፡ የጎንደርና አካባቢው ችግር እየተወሳሰበና በቀላሉም ሊፈታ የማየችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ከቦታው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ዛሬ ሐምሌ 30 ቀን 2008 ዓ.ም. አንድ የትግራይ ተወላጅ የሆነ ወያኔ ለተጋድሎ በወጡ ዐማሮች ላይ ቦንብ በመወርወር ከሦስት በላይ ሰዎችን ገደለ፡፡ የወያኔ መከላከያ ሠራዊት ይህን ነፍሰ በላ ሰው ተከላክለው ለማዳን ቢሞክሩም አልቻሉም፤ ከነቤቱ መቃጠሉን ለማወቅ ተችሏል። ይህን ተከትሎ የሥርዓቱ አገልጋይ የሆኑ የትግራይ ተወላጆችን መንግሥታቸው በአየር መንገድ በኩል ሲያጓጉዝ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ዛሬ ከጎንደር አጼ ቴዎድሮስ አየር ማረፊያ ወደ መቀሌና አዲስ አበባ በርካታ የትግራይ ተወላጆች መውጣታቸውን ለማረጋገጥ ችለናል፡፡
አዘዞ – በአዘዞ ትናንት የተሰው ሰማእታትን ለመቅበር በሚሔዱ ሰዎች ላይ የተኩስ እሩምታ የከፈተው መከላከያ ሠራዊት ሞትን የማይፈሩት የዐማራ ወጣቶች አዘዞ የሚገኘውን የመከላከያ ሠራዊት ካምፕ መቆጣጠራቸው ተሰምቷል፡፡ የሥርዓቱ አገልጋይ የሆኑ ግለሰቦች የሆኑ የንገድ ተቋማት በብዛት መውደማቸው የታወቀ ሲሆን ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ የተኩስ ልውውጥ መኖሩን ለማወቅ ችለናል፡፡
ቆላድባ፡- በደንቢያ ወረዳ የቆላ ድባ ዐማሮች ተጋድሎ ከሁሉም ያየለ እንደነበርም ሰምተናል፡፡ በሌሊት በቁጣ የወጣው የደንቢያ ዐማራ ማንም የሚያቆመው ኃይል ሳይኖር የሥርዓቱ መገልገያ የነበሩ ተቋማትንና ተሸከርካሪዎችን ዶጋ አመድ አድርጓል፡፡ እስካሁን ባለመን መረጃ መሠረት ከዐሥር ያላነሱ መኪናዎች ተቃጥለዋል፤ የብአዴን፣ የአብቁተና ሌሎችም መሥሪያ ቤቶች ወድመዋል፡፡ ከወያኔ መከላከያ ሠራዊት ጋር በበነበረ ተጋድሎ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ዐማሮች የቆሰሉ ሲሆን የሞቱ ሰዎች መኖር አለመኖራቸው የደረሰን መረጃ የለም፡፡
አይባ- ከጭልጋ ሰራባ ካምፕ ወደ ጎንደር በመጓዝ ላይ ከነበረ የትግሬ መከላከያ ጋር በተደረገ ተጋድሎ አይባ ላይ ሁለት ያክል ዐማሮች ተሰውተዋል፡፡
አርማጭሆ፡- በላይ፣ ታችና ምእራብ አርማጭሆ፣ በጠገዴና በጠረፍ አካባቢዎች ዐማሮች አካባቢያቸውን ነጻ ማውጣታቸውን የተሰማ ቢሆንም የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ በመቋረጡ ማረጋገጥ አልተቻለም፡፡ የሱዳን መንግሥት በምዕራብ አርማጭሆ በኩል ከዐማሮች ላይ ጦርነት መጀመሩን የተሠማ ቢሆንም እስካሁን በስልክ ችግር ማረጋገጥ አልተቻለም (ዜናውን የጠናቀረው ሰው ማረጋገጥ አልቻለም)፡፡
ጋይንት፡- የነፋስ መውጫ ከተማ ዛሬ ከዝናብ ጋር ተጋድሎዋን በጠዋት ነበር የጀመረችው፡፡ ነፋስ መውጫ ዐማሮች ትናንት የታሰሩ ዐማሮችን አስፈትተው ንብረትነቱ የወያኔ የሆነን የእንጨት ክምር አቃጥለዋል፡፡ የክልሉ ፖሊስ አብሮ ለተጋድሎ መሠለፉን ብንሰማም በኋላ ላይ ቁጥራቸው ያልታወቀ ለተጋድሎ የወጡ ወጣቶች መሰዋታቸው ተነግሯል፡፡ ዜናውን ያጠናቀረው ስንት ሰዎች መስዋት እንደሆኑ ሊያወቅ አልቻለም፡፡

No comments:
Post a Comment