ETHIOPIAN Revolution
Monday, July 20, 2020
Friday, August 17, 2018
ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአማራ ክልል ጉብኝት እንደሚያደርጉ ተገለጸ።
የመጀመሪያ የ3 ክፍል ዶክተር አይ ደ/ር ቢቸግር
(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 11/2010)የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአማራ ክልል ጉብኝት እንደሚያደርጉ ተገለጸ።
(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 11/2010)የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአማራ ክልል ጉብኝት እንደሚያደርጉ ተገለጸ።
በፕሬዝዳንቱ የሚመራው የልኡካን ቡድን ወደ አማራ ክልል እንደሚመጣ የአማራ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ሃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ናቸው።
በአስመራ ቆይታ ያደረገው የአማራ ክልል የልኡካን ቡድን ከአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ አመራሮች ጋር መወያቱ ታውቋል።
ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በአማራ ክልል የሚያደርጉት ጉብኝት መቼና በምን ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር እንደሚሆን ግን በዝርዝር አልተገለጸም።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ41 አመት በኋላ ወደ ሞቃዲሾ በረራ ሊጀምር ነው ተብሏል።
የአማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን እንደገለጹት ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ አማራ ክልል በመምጣት ጉብኝት እንዲያደርጉ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
የሕዝባዊ ግንባር ለዴሞክራሲና ፍትህ የፖለቲካ ዘርፍ ሃላፊ እና የፕሬዝዳንት ኢሳያስ ልዩ አማካሪ ከሆኑት ከአቶ የማነ ገብረአብ ጋር
ጉብኝቱ መቼና በምን ጉዳይ ላይ እንደሚያተኩር ግን ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል። አቶ ኢሳያስ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ለ20 ዓመታት ተቋርጦ የነበረው ግንኙነት በአዲስ መልክ ከተጀመረ ወዲህ ኢትዮጵያን ሲጎበኙ የአማራ ክልሉ ለሁለተኛ ጊዜ ሆኖ ይመዘገባል።
የአማራ ክልል ልዩ የልዑካን ቡድንም ወደ ኤርትራ በቅርቡ እንደሚያመራ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ገልጸዋል።
አቶ ንጉሱ ሰሞኑን የክልላቸውን መንግስት ወክለው አንድ የልዑካን ቡድን በመምራት አስመራ ቆይታ ማድረጋቸው መዘገቡ ይታወሳል።
በዚህን ወቅት በኤርትራ ብረት አንስቶ እየታገለ ከሚገኘው የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ ጋር መወያያቱ ተገልጿል።
ንቅናቄው ወደ ሀገር ቤት በመግባት በሰላማዊ መንገድ ትግሉ እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ መደረሱንም አቶ ንጉሱ ጥላሁን አስታውቀዋል።
በኤርትራ ቆይታ ወቅት ከሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ምክክር መደረጉን የጠቀሱት አቶ ንጉሱ ጥላሁን በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት መደረጉም ተመልክቷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሶማሊያ በረራ ሊጀመር መሆኑ ተገልጿል።
ወደ ሞቃዲሾ የሚደረገው በረራ ከ41 ዓመታት በኋላ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን በሳምንት ሶስት ጊዜ እንደሚደረግም ለማወቅ ተችሏል።
ከሶማሊያ ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት በጅቡቲና በናይሮቢ ሲደረግ የነበረውን በረራ የሚያስቀረው የሞቃዲሾው አዲሱ መስመር መቼ እንደሚጀመር ግን የተገለጸ ነገር የለም።
Tuesday, August 7, 2018
Friday, September 29, 2017
Friday, May 5, 2017
ጥቂት ስለአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊ አርበኛ ሃና – ከጋዜጠኛ መሳይ መኮንን
የማህሌትንና የኤዶምን ከህወሀት ማጎሪያ እስር ቤት ነጻ መሆን ውስጤ የፈጠረውን ደስታ እያጣጣምኩ እያለ ድንገት በትዝታ አምስት ወራት ወደ ሁዋላ ሄድኩኝ- -ከኤርትራ በረሃ:: ይህቺን ኢትዮጵያን ከህወሀት እስር ቤት ነጻ ለማውጣት ብረት ያነሳችውን እህታችንን ላስተዋውቃችሁ::
አርበኛ ሀና ትባላለች:: የ23 ዓመት ወጣት ናት:: የአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊ ወታደር ስትሆን በተለያዩ አውደ ውጊያዎች ተሳትፋለች:: በኤርትራ በረሃ ስማቸው ከጀግንነት ጋር ከሚነሳላቸው አርበኞች መሃል ሀና ግንባር ቀደም ናት:: ስሟ በአርበኞች መንደር ገኖ ይነሳል::
………አንድ ጊዜ ላይ እንዲህ ሆነ::
አርበኛ ሀና ትባላለች:: የ23 ዓመት ወጣት ናት:: የአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊ ወታደር ስትሆን በተለያዩ አውደ ውጊያዎች ተሳትፋለች:: በኤርትራ በረሃ ስማቸው ከጀግንነት ጋር ከሚነሳላቸው አርበኞች መሃል ሀና ግንባር ቀደም ናት:: ስሟ በአርበኞች መንደር ገኖ ይነሳል::
………አንድ ጊዜ ላይ እንዲህ ሆነ::
ሀና የምትገኝበት ወታደራዊ ክፍል ግዳጅ ይሰጠዋል:: እስከ 30 የሚጠጋ አርበኛ የሚገኝበት ይህ ቡድን የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጦ በመግባት በአንድ የህወሀት ወታደራዊ ካምፕ ላይ ጥቃት ፈጽሞ የመመለስ ግዳጅ ተሰጥቶት ይሰማራል:: ሀና መትረየሷን ታጥቃለች:: ጠዋት ከመነሻቸው ወደ ኢላማ ቦታው ገሰገሱ:: እንደታቀደው ድንገተኛ ጥቃቱ ተሰንዝሮ የታሰበውን ጉዳት አድርሰው ወደ ካምፓቸው ሊመለሱ እያለ ድንገት በህወሀት ሰራዊት ይከበባሉ:: ምን ይደረግ? ብዙ ቁጥር ያለውንና እስከአፍንጫው የታጠቀውን የህወሀት ሰራዊት መክቶ ወደ ካምፕ መመለስ ከባድ ሆነ:: የዚህን ጊዜ ነበር አንድ ጀግና ታሪክ የሰራችው:: ….ሀና::
መትረየሷን መተረች:: ገዢ መሬት ያዘች:: ቦታዋን አስተካከለች:: ….እሷ መስዋዕት ሆና የትግል ጓዶቿን ልታስመልጥ ወሰነች:: ምሽት እየመጣ ነው:: ጓዶቿ ተስናበቷት:: ዳግም በህይወት እንደማያገኟት ታወቃቸው:: …እሷ መትረየሷን ወደ ህወሀት ሰራዊት ለቀቀችው:: ለጓዶቿ ሽፋን በሚሰጥ ስልት አስካካችው:: …ፍልሚያው በአንዲት ሀና እና በህወሀት ሰራዊት መሃል ሆነ:: የሀና መትረየስ ያስካካል:: ጓዶች በዚያ ሽፋን ወደ ጦር ካምፓቸው እየተመለሱ ነው:: የሀና የመትረየስ ድምጽ እየራቃቸው ነው:: እነሱ ይተርፉ ዘንድ አንድ አርበኛ መስዋዕት መሆን ግድ አለ:: በተሰጣቸው ግዳጅ ውጤታማነት እየተደሰቱ የሃናን መስዋዕትነት እያወደሱ ከካምፓቸው ምሽት ላይ ደረሱ:: በአርበኞች መንደር ህይወት እንዲህ ናት:: ታጋይ ይሰዋል:: ትግል ይቀጥላል::
…እኩለ ሌሊት ከመድረሱ በፊት ነው:: ጭው ካለው የኤርትራ በረሃ አንድ ሰው ወደ አርበኞቹ መንደር ከኢትዮጵያ ድንበር አቅጣጫ ይገሰግሳል:: በርቀት የተመለከቱት የሌሊት የካምፕ ተረኛ ዋርዲያዎች(ጠባቂዎች) መሳሪያቸውን አስተካክለው ጣት ከቃታ አገናኝተው ወደ ካምፑ እየገሰገሰ ያለውን ሰው ይጠብቃሉ:: ውድቅት ሌሊት ስለነበር ማንነት መለየት አልተቻለም:: የሚገሰግሰው ሰው እየቀረበ ሲመጣ ዋርዲያዎቹም ኢላማቸውን አስተካክለው እርምጃ ለመውሰድ ተዘጋጁ:: ….ሰውዬው ቀረበ:: ሴት ናት::ሃና:: ዋርዲያዎቹ አላመኑም:: የዕለቱን የይለፍ ቃል ጠየቋት:: መለሰችላቸው:: ደክሟታል:: ተአምር የሚያሰኘው ከዚይ የህወሀት ሰራዊት ከበባ ማምለጧ አይደለም:: ሁለት የጦር መሳሪያዎችንም ማርካ ተሸክማለች:: ከሷ መትረየስ ጋር ሶስት:: ዋርዲያዎቹ በሚያዩት ነገር ተደንቀዋል:: በአርበኞች መንደር ስለ ሃና እርም ወጥቷል:: ጉድ ተባለ::
….ሃናን በአካል ሳገኛት በጣም ቁጥብ ነበረች:: ብዙ አትናገርም:: ታሪኳን እንድታጫውተኝ ያደረኩት ጥረት አልተሳካም:: ሲበዛ ዝምተኛ ናት:: ጀግና አይናገርም::
…ሃና ከሰሞኑ ውጊያዎች በአንዱ እንደተሰለፈች እገምታለሁ:: ልብን በኩራት በሚያሞቀው ጀግንነቷ ሁሌም አስታውሳታለሁ:: የጣይቱ ልጅ!!!!!
…ሃና ከሰሞኑ ውጊያዎች በአንዱ እንደተሰለፈች እገምታለሁ:: ልብን በኩራት በሚያሞቀው ጀግንነቷ ሁሌም አስታውሳታለሁ:: የጣይቱ ልጅ!!!!!

Subscribe to:
Posts (Atom)